Saturday, 12 August 2017 00:00

ኢትዮጵያውያንና ሶማሊያውያን ስደተኞች ወደ ባህር ተጥለው መሞታቸው አሣዛኝ ሆኗል

Written by 
Rate this item
(5 votes)

በየመን የባህር ዳርቻ በህገ ወጥ የሰዎች አዘዋዋሪዎች 120 ኢትዮጵያውንና ሶማሊያውያን ሆን ተብሎ ከጀልባ ላይ ወደ ባህር ተጥለው 50 የሚደርሡ ሰዎች መሞታቸው የአለም መገናኛ ብዙሃንን መነጋጋሪያ ሆኗል፡፡
አለማቀፉ የስደተኞች ድርጅትን (IOM) ጠቅሶ ዘገባውን ያሠራጨው ሲኤንኤን ረቡዕ እለት ወደ የመን እያመራች ባለች ጀልባ የተሣፈሩ 120 ኢትዮጵያዊያንና ሶማሊያውያን በአዘዋዋሪዎቹ ወደ ባህሩ ተጥለዋል ብሏል፡፡
በዚህም  50 ያህሉ መሞታቸው ሲረጋገጥ፣ 22ቱ የደረሱበት አለመታወቁን እንዲሁም 29ኙ በአይኦ ኤም የነፍስ አድን ሰራተኞች ህይወታቸው መትረፉ ተዘግቧል።
የስደተኞቹ አማካይ እድሜ 16 አመት መሆኑን የጠቆመው አይኦኤም፤ የታዳጊዎች ስደት መበራከት አሳሳቢ መሆኑን አስታውቋል፡፡  ከጥር 2009  ጀምሮ 55 ሺህ ያህል የምስራቅ አፍሪካ ዜጎች በየመን አቋርጠው ወደ መካከለኛው ምስራቅ ሃገራት መግባታቸውን የሚጠቁመው የስደተኞች ድርጅቱ ሪፖርት፤ ከነዚህም ውስጥ 30 ሺህ ያህሉ እድሜያቸው ከ18 ዓመት በታች፣ ሲሶ ያህሉም ሴቶች መሆናቸውን ያመለክታል፡፡

Read 1209 times