Sunday, 06 August 2017 00:00

“የሰላም መዝሙር ለኢትዮጵያና ለኤርትራ ህዝቦች” የሙዚቃ ኮንሰርትና የፓናል ውይይት ይካሄዳል

Written by 
Rate this item
(2 votes)

   ‹‹የሰላም መዝሙር ለኢትዮጵያና ለኤርትራ ህዝቦች” የተሰኘ የሙዚቃ ኮንሰርትና የፓናል ውይይት ሊካሄድ ነው፡፡ የሙዚቃ ኮንሰርቱንና የፓናል ውይይቱን የሚያዘጋጀው “ሰለብሪቲ ኤቨንትስ” ባለፈው ሳምንት በሰጠው ጋዜጣዊ መግለጫ፣ የሁለቱን አገራት ህዝቦች የቀደመ ግንኙነት ወደተሻለ ደረጃ ለማድረስ ያግዛል ያለውን የሙዚቃ ድግስና የፓናል ውይይት የሚያካሂደው በቀጣዩ ዓመት ህዳር ወር ላይ ሲሆን በሙዚቃ ኮንሰርቱ ታዋቂና ዝነኛ የሁለቱ አገራት ድምፃውያን ይሳተፋሉ ተብሏል፡፡
በፓናል ውይይቱ ላይ የታሪክ ምሁራን፣ የአገር ሽማግሌዎች፣ የማህበረሰብ ሰራተኞች የመንግስትና የተቃዋሚ ፓርቲ ተወካዮች በአጠቃላይ 800 ሰዎች የሚሳተፉ ሲሆን በሁለቱ አገር ህዝቦች የወደፊት ግንኙነት ላይ ይመካከራሉ ተብሏል፡፡ የኮንሰርቱና የፓናል ውይይቱ አላማ የሁለቱ አገራት ህዝቦች ድንበርና ጥበቃ ሳይገድባቸው በችግር ጊዜ አብሮ የመቆምና የመደጋገፍ ባህልን እንዲያዳብሩ፣ እንዲሁም የቀደመ ግንኙነታቸው እንዲጠናከር ያለመ መሆኑን የሰለብሪቲ ኤቨንትስ ዋና ስራ አስኪያጅ አቶ ሀብቶም ገ/ስላሴ ለጋዜጠኞች ተናግረዋል፡፡
የፓናል ውይይቱ በመጪው ህዳር 17 የሚካሄድ ሲሆን ኮንሰርቱ ህዳር 30 በሚሊኒየም አዳራሽ እንደሚካሄድ አቶ አብርሃም ተናግረዋል፡፡ በሙዚቃ ኮንሰርቱ ላይ በኢትዮጵያ በአራቱ መጠለያዎች የሚገኙ የኤርትራ ስደተኞችም ይታደማሉ ተብሏል፡፡

Read 5267 times