Saturday, 22 July 2017 15:54

“የሚስት ምርቃት” መፅሐፍ ለንባብ በቃ

Written by 
Rate this item
(2 votes)

  በደራሲ ተስፋዬ አለነ የተሰናዳው “የሚስት ምርቃት” ልብ ወለድ መፅሐፍ ለንባብ በቃ፡፡ መፅሐፉ በጥቅሉ በፍቅር፣ በማህበራዊና በፖለቲካ ጉዳዮች ላይ
የሚያጠነጥኑ 20 አጫጭር ልብ ወለድ ታሪኮችን ያካተተ ሲሆን ከዚያ ውስጥ “ስደተኛው ፍቅር” የተሰኘው ታሪክ ግን በእውነተኛ ታሪክ ላይ ያተኮረ መሆኑን ደራሲው ተናግሯል፡፡ በ216 ገፅ የተመጠነው መፅሐፉ በ61 ብር ከ20 ሳንቲም ለገበያ የቀረበ ነው፡፡ አምስተኛ ስራውን ሰሞኑን ለአንባቢ ጀባ ያለው ደራሲ ተስፋዬ አለነ በተለያዩ ጋዜጦችና መፅሄቶች አዝናኝ ወጎችን በመፃፍ የሚታወቅ ሲሆን ከዚህ ቀደምም “የመንጌ ውሽሚት”፣ “እንክልካይ”፣ “ዘላለማዊ ጓደኝነት” እና “Effective English” የተሰኙ መፅሐፍትን ለንባብ ማብቃቱ ይታወቃል፡፡

Read 3045 times