የኢትዮጵያ ሠራተኞችን ትግል የሚዳስሰው መፅሐፍ ዛሬ ይመረቃል፡፡ ከቀኑ 8 ሰዓት ሜክሲኮ አደባባይ አካባቢ በሚገኘው የአዲስ አበባ ንግድ ምክር ቤት አዳራሸ የሚመረቀው “የኢትዮጵያ ሠራተኞች አንድነት ማህበር፣ ውልደት፣ ዕድገት፣ ውድቀት” የተሰኘው ይኸው መፅሐፍ ከአፄ ኃይለሥላሴ እስከ ደርግ ያለውን የታሪክ ሁነት ይሸፍናል፡፡ በፎቶግራፎች ጭምር የተደገፈው የአቶ በየነ ሰሎሞን ባለ 261 ገፅ መፅሐፍ ዋጋ 50.00 ብር ሲሆን መጽሐፉ ከትናንት ወዲያ ጀምሮ ለንባብ በቅቷል፡፡