Saturday, 08 July 2017 12:58

የኮሌራ ወረርሽኝ ከ1ሺህ 600 በላይ የመናውያንን ገድሏል

Written by 
Rate this item
(3 votes)

 በእርስ በእርስ ጦርነት በምትታመሰዋ የመን የተከሰተው የኮሌራ ወረርሽኝ ባለፉት ሶስት ወራት ጊዜ ውስጥ ከ1ሺህ 600 በላይ የመናውያንን ለህልፈተ ህይወት መዳረጉን የተባበሩት መንግስታት ድርጅት ከትናንት በስቲያ አስታውቋል፡፡ ወረርሽኙ በስፋት በመሰራጨት ሁሉንም የአገሪቱ ግዛቶች ማዳረሱን ያስታወቀው ተመድ፣ ከ270 ሺህ ያህል ዜጎችም የኮሌራ ተጠቂ ሳይሆኑ እንዳልቀሩ መገመቱን ገልጧል፡፡ የአለም የጤና ድርጅት ወረርሽኙን ለመግታትና
ታማሚዎችን በአግባቡ ለማከም ከአጋር ድርጅቶች ጋር እየሰራ እንደሚገኝ ያስታወቁት የተመድ ቃል አቀባይ ስቴፋኒ ጃሪክ፣ ባለፈው ማክሰኞ 400 ቶን ያህል የህክምና ቁሳቁስና መድሃኒት ማግኘቱን ጠቁመዋል፡፡ በኮሌራ የተጠቁ የመናውያንን ለማከም በአገሪቱ የተለያዩ አካባቢዎች 600 ያህል ጊዚያዊ ጣቢያዎች እንደሚቋቋሙም አመልክተዋል፡፡

Read 890 times