Sunday, 09 July 2017 00:00

ከአሊ ቢራ እስከ አቢ ላቀው የሚያቀነቅኑበት ኮንሰርት - በሚሊኒየም አዳራሽ

Written by 
Rate this item
(16 votes)

  የአስቸኳይ ጊዜ አዋጁን ድንጋጌዎች በመተላለፍ ህገ መንግስታዊ ስርአቱን በኃይል ለማስወገድ ተንቀሳቅሰዋል በሚል የተከሰሱት አንጋፋው ፖለቲከኛ ዶ/ር መረራ ጉዲና፤ የምስክሮችን ዝርዝር የማወቅ መብትን” በተመለከተ ያቀረቡት የክስ መቃወሚያ ላይ የፌዴሬሽን ም/ቤት የህግ ትርጉም እንዲሰጥበት ፍ/ቤቱ ብይን ሰጠ፡፡
ዶ/ር መረራ ጉዲና ለፍ/ቤቱ ካቀረቧቸው የክስ መቃወሚያዎች መካከል ‹‹ክሱ የተሟላ አይደለም፤ ክሱ ፖለቲካዊ ነው፤ በሽብር ክስ ሳልከሰስ የሽብር ክስ ማስረጃ ሊጠቀስብኝ አይገባም›› የሚሉና ሌሎች የክስ መቃወሚያ በጠበቆቻቸው በኩል ያቀረቡ ቢሆንም ከአንዱ በስተቀር ቀሪዎቹን መቃወሚያዎች ፍ/ቤቱ ትናንት በዋለው ችሎት እንዳልተቀበላቸው አስታውቋል፡፡
ዶ/ር መረራ ጉዲና የተከሰሱት በአስቸኳይ ጊዜ አዋጁ የማስፈፀሚያ ደንብና በወንጀለኛ መቅጫ ህግ አንቀፅ ነው፡፡ የማስረጃ ዝርዝሩ የቀረበበባቸው ደግሞ በፀረ ሽብር አዋጁ መሰረት መሆኑን የዶ/ር መረራ የህግ አማካሪና ጠበቃ አቶ ወንድሙ ኢብሣ ለአዲስ አድማስ አስረድተዋል፡፡ በሽብር የተከሰሰ ሰው፤ የሰው ምስክሮች ላይገለጡለት እንደሚችል በህግ ተደንግጓል፡፡
ተከሳሹ በሽብር ወንጀል አለመከሰሳቸውን በመጥቀስ የሰው ማስረጃ ዝርዝሮች እንዲገለጥላቸው ጥያቄ በማቅረባቸው ፍ/ቤቱ የህግ ትርጉም ያስፈልገዋል ሲል ፌዴሬሽን ም/ቤት የህግ ትርጉም እንዲሰጥበት ብይን ሊሰጥ መቻሉን አቶ ወንድሙ አብራርተዋል፡፡
የፌዴሬሽን ም/ቤትን የህግ ትርጉም ለመጠባበቅ ጉዳዩ ለሐምሌ 25 ቀን 2009 ዓ.ም ተቀጥሯል፡፡
ዶ/ር መረራ ፍ/ቤት የመናገር እድል እንዲሰጣቸው ጠይቀው ባደረጉት ንግግር፤ “የኔ ክስ የፖለቲካዊ ክስ ነው፣ ለኦሮሞ ህዝብ መብት በመታገሌ ነው የተከሰስኩት፣ ለመላ የኢትዮጵያ ህዝቦች ነፃነት በመቆሜ ነው፤ ለሃቀኛ ፌደራል ስርአት መገንባትና ነፃ ፍ/ቤት፣ ነፃ የዳኝነትና የፍትህ ስርአት እንዲፈጠር ስለታገልኩ ነው የተከሰስኩት፡፡
ይሄን ትግል እኔ ብቻ አይደለሁም የታገልኩት፤ ቀደም ሲል አቤ ጉበኛ የሚባል ደራሲ “አልወለድም” የሚል መፅሃፍ ፅፎ ለንጉሡ ማስጠንቀቂያ ነግሮ፣ ንጉሡ ሳይሰማቸው መጨረሻው እንደዛ ሆነ፤ በደርግ ስርአት ደግሞ በአሉ ግርማ “ኦሮማይ” የሚል መፅሐፍ ፅፎ ለደርግ መንግስት ምክር ቢሰጥ ሳይሰማ ቀርቶ የሆነውን ታሪክም ፍ/ቤቱም ያውቃል፤ እኔ ደግሞ “የተራበ ህዝብ መሪዎቹን ይበላል” ብዬ መፅሓፍ ፅፌያለሁ፤ እባካችሁ ዳኞች ለታሪክ ስትሉ እነዚህን ሶስት መፅሃፎች አንብቡ …. የሰራሁት ወንጀል የለም፡፡ ለሁላችንም የምትሆን ህግና የህግ የበላይነት የሰፈነባት ሰው ሁሉ በእኩል የሚኖርባትን ሀገር እንመስርት ብዬ አንድ ለሆዱ ከሚያስብ ምሁር በላይ ዋጋ በመክፈሌ ነው የተከሰስኩት” ማለታቸው ታውቋል፡፡






Read 6882 times