እየው ኖርን ሳንዋደድ፣ እድሜም ገፋ እንደ ዘበት፣
ለሰው ይምሰል ጥላችንም፣ እንደፍቅር ተወራለት፡፡
ባንድ ማድ፣ እየበላን እየጠጣን፣
ለሚያየን አስጎምጅተን፣ እያስቀናን፤
አለን ሳንተኛ፣ ሳናንቀላፋ፣
እኛው በኛ፣ ስንጋፋ፡፡
ቆቅ ሆነን፣ ስንጠባበቅ፣
ደግሞ- የዋህ መስለን ስንሳሳቅ፤
ብዙ…. ብዙ! ዘመን፣ ተቆጠረ፣
ቂም ሳይፈታ፣ እንደከረረ!፡፡
ጋሻው ሙሉ
Published in
ጥበብ