የአገሪቱ መንግስት የቅንጦት መኪና መጠቀም መብታቸው ነው ብሏል
በሞዛምቢክ የፓርላማ አባላት ለሆኑ የገዢው ፓርቲና የተቃዋሚ ፓርቲ ከፍተኛ ባለስልጣናት በ3.8 ሚሊዮን ዶላር ወጪ 18 ዘመናዊ መርሴድስ ቤንዝ የቅንጦት መኪኖች መገዛታቸው፣ በአገሪቱ ዜጎች ዘንድ ከፍተኛ ቁጣ መቀስቀሱን ቢቢሲ ዘግቧል፡፡
የአገሪቱ መንግስት ለፓርላማ ቋሚ ኮሚቴዎች አመራሮች አገልግሎት ይሰጡ ዘንድ ከፍተኛ ገንዘብ ወጪ አድርጎ ውድ መኪኖችን መግዛቱ፣ በተለይም የማህበራዊ ድረገጽ ተጠቃሚ በሆኑ የአገሪቱ ወጣቶች፣ ከፍተኛ ተቃውሞ እንደገጠመው ዘገባው ገልጧል፡፡
በርካታ የማህበራዊ ድረገጽ ተጠቃሚ ሞዛምቢካውያን፣ “አገሪቱ በከፋ የፋይናንስ እጥረት በተጠቃችበት በዚህ አስቸጋሪ ወቅት ይህን ያህል ገንዘብ አውጥቶ፣ የቅንጦት መኪና መግዛት፣ በዜጎች ላይ መቀለድ ነው” በሚል ድርጊቱን በስፋት አውግዘውታል፡፡ የአገሪቱ ተቃዋሚ ፓርቲ አመራሮች፣ ቡድኖችና የሲቪክ ማህበራት ድርጊቱን በጽኑ ቢቃወሙትም፣ የአገሪቱ ብሄራዊ የበጀት ቢሮ ዳይሬክተር ሮግሪዮ ንኮሞ ግን፣ የፓርላማ ቋሚ ኮሚቴዎች አመራሮች፣ ”የቅንጦት መኪና መጠቀም መብታቸው ነው” ሲሉ ትችቱን ማጣጣላቸውን ዘገባው አክሎ ገልጧል፡፡
Wednesday, 21 June 2017 00:00
ሞዛምቢካውያን፤ በ3.8 ሚ. ዶ. በተገዙት የባለስልጣናት የቅንጦት መኪኖች ተቆጥተዋል
Written by Administrator
Published in
ከአለም ዙሪያ
Latest from Administrator
- የእስራኤል እና የኢራን ፍጥጫ
- Insights on Israel's Response: Interview with Mr. Tomer Bar-Lavi, Chargé d’Affaires at the Embassy of Israel to Ethiopia
- Barr, a vocal Trump critic, says he will ‘support the Republican ticket’ in November
- Iran president warns of ‘massive’ response if Israel launches ‘tiniest invasion’
- "አልሞቷል" ፊልም ዛሬ በዓለም ሲኒማ ይመረቃል