Wednesday, 14 June 2017 00:00

ስዊዘርላንዳዊው በ6 “የፌስቡክ ላይክ” 4 ሺህ ዶላር ተቀጣ

Written by 
Rate this item
(1 Vote)

  በፌስቡክ በተሰራጨ አንድ ጽሁፍ ላይ የተሰጡና ያለአግባብ የአንድን ግለሰብ ስም የሚያጠፉ ናቸው የተባሉ ስድስት  አስተያየቶችን ላይክ ያደረገው ስዊዘርላንዳዊ፣ ዙሪክ ውስጥ በሚገኝ ፍርድ ቤት ውሳኔ የ4 ሺህ 100 ዶላር ቅጣት እንደተጣለበት አጃንስ ፍራንስ ፕሬስ ዘግቧል፡፡
የ45 አመቱ ስዊዘርላንዳዊ በአገሪቱ የሚሰራ አንድ የእንስሳት ተንከባካቢ ቡድን ሃላፊ የሆኑትን ኤርዊን ኬስለር የተባሉ ግለሰብ በተመለከተ በፌስቡክ በተሰራጨ ጽሁፍ ላይ የተሰጡ ስም አጥፊና ሃሰተኛ አስተያየቶችን ላይክ በማድረግ ብዙ የፌስቡክ ተጠቃሚዎች እንዲመለከቷቸውና እውነት አድርገው እንዲቀበሏቸው በማድረጉ ጥፋተኛ ነው በሚል ፍርድ ቤቱ ቅጣቱን እንደጣለበት ዘገባው ገልጧል፡፡
ኤርዊን ኬስለር፤ “መሰረተ ቢስ በሆኑ ሃሰተኛ መረጃዎች ላይ የተመሰረቱና ያለ አግባብ ስሜን የሚያጠፉ የፌስቡክ ጽሁፎችንና አስተያየቶችን ላይክ በማድረግ ህገወጥ ወንጀል ፈጽመውብኛል” በሚል አስራ አምስት ያህል የፌስቡክ ተጠቃሚዎችን መክሰሳቸውንም ዘገባው አስረድቷል፡፡

Read 2825 times