Sunday, 28 May 2017 00:00

የቻይና የህዝብ ቁጥር ተጭበርብሯል፤ የህንድ ይበልጣል ተባለ

Written by 
Rate this item
(1 Vote)

  የህንድ ህዝብ 1.32 ቢሊዮን ሲደርስ፣ የቻይና ግን 1.29 ቢሊዮን ቢደርስ ነው ተብሏል

     የቻይና የህዝብ ቁጥር ሆን ተብሎ በመጋነን በ90 ሚሊዮን ያህል እንዲጨምር መደረጉንና 1.32 ቢሊዮን ህዝብ ያላት ህንድ በቻይና ተይዞ የነበረውን የዓለማችን የህዝብ ብዛት ደረጃ መረከብ እንደምትችል በጥናት ማረጋገጣቸውን አንድ ታዋቂ  የስነ ህዝብ ተመራማሪ ማስታወቃቸውን ዘ ጋርዲያን ዘግቧል፡፡
በአሜሪካው የዊስከንሰን ማዲሰን ዩኒቨርሲቲ የስነ ህዝብ ተመራማሪ የሆኑትና በህንድ እና በቻይና የህዝብ ብዛት ዙሪያ ጥናት ሲሰሩ የቆዩት ዪ ፉክሲያን፣ የቻይና ባለሙያዎች በህዝብ ቆጠራ ወቅት ሆን ብለው የህዝቡን ቁጥር እንዳጋነኑት በመጠቆም የአገሪቱ ህዝብ ቁጥር በ90 ሚሊዮን እንዲጨምር ማድረጋቸውን ገልጸዋል፡፡
የቻይና የህዝብ ቁጥር የአገሪቱ መንግስት እንደሚለው 1.38 ቢሊዮን ሳይሆን፣ ከዚያ ያነሰ ነው፤ የህዝብ ቁጥሩ እስካለፈው የፈረንጆች አመት 2016 መጨረሻ ቢበዛ 1.29 ቢሊዮን ያህል ቢደርስ ነው፤ በመሆኑም ህንድ በህዝብ ብዛት ከቻይና በመቅደም በአንደኛነት እንድትቀመጥ ያደርጋታል ብለዋል - ተመራማሪው፡፡
ተመራማሪው ይህን ቢሉም በርካታ ህንዳውያንና ቻይናውያን የስነህዝብ ባለሙያዎች ግን የተመራማሪውን ድምዳሜ በበቂ መረጃዎች ላይ ያልተመሰረተና ስሜታዊነት የሚንጸባረቅበት፣ ሙያዊ ያልሆነ አደገኛ ነገር ነው በማለት በስፋት እያጣጣሉት እንደሚገኙም ዘገባው ገልጧል፡፡

Read 5463 times