Sunday, 21 May 2017 00:00

ፌስቡክ በአውሮፓ ህብረት 95 ሚ. ፓውንድ ተቀጣ

Written by 
Rate this item
(0 votes)

ፌስቡክ ታዋቂው የማህበራዊ ድረ ገጽ ዋትሳፕን የራሱ ለማድረግ ካከናወነው ግዢ ጋር በተያያዘ ለአውሮፓ ህብረት የተሳሳተ መረጃ ሰጥቷል በሚል በህብረቱ የንግድ ውድድር ተቆጣጣሪ አካላት 95 ሚሊዮን ፓውንድ ቅጣት እንደተጣለበት ዘ ጋርዲያን ዘግቧል፡፡
ፌስቡክ ከሶስት አመታት በፊት ዋትሳፕን በ19 ቢሊዮን ዶላር በመግዛት የራሱ ባደረገበት ወቅት የሁለቱን ማህበራዊ ድረገጾች ተጠቃሚዎች ኣካውንቶች ግንኙነት በተመለከተ ለህብረቱ ከሰጣቸው መረጃዎች ጋር በሚቃረን መልኩ ሲሰራ መገኘቱ በመረጋገጡ ቅጣቱ እንደተጣለበት ዘገባው ገልጧል፡፡
ፌስቡክ የራሱንና የዋትሳፕ ተጠቃሚዎችን አካውንቶች የግዢ ውሉ ላይ ከተጠቀሰው ውጭ ከስልክ ቁጥራቸው ጋር አስተሳስሮ አገልግሎት ሲሰጥ መቆየቱ ስህተት መሆኑን በማመን፣ ድርጊቱ ሆን ተብሎ የተፈጸመ አይደለም ሲል ቅጣቱ መተላለፉን ተከትሎ ባወጣው መግለጫ አስተባብሏል፡፡
ኩባንያው ድርጊቱን ሆን ብዬ አልፈጸምኩም ብሎ ያስተባብል እንጂ የተጣለበትን ከፍተኛ የገንዘብ ቅጣት በመቃወም ይግባኝ ይጠይቅ አይጠይቅ በግልጽ ያስታወቀው ነገር እንደሌለም ዘገባው አክሎ ገልጧል፡፡

Read 1104 times