Friday, 07 April 2017 00:00

ትራኮን የመፅሐፍት አውደ ርዕይና የሂስ ጉባኤ ዛሬና ነገ ይካሄዳል

Written by 
Rate this item
(0 votes)

 በወሩ መጨረሻ ባሉት ቅዳሜና እሁድ የሚካሄደው ትራኮን የመፅሀፍት አውደ ርዕይና የሂስ ጉባኤ፤ ዛሬና ነገ ጥቁር አንበሳ ፊት ለፊት በሚገኘው ትራኮን ታወር ይካሄዳል፡፡ ዛሬ ከቀኑ 8፡00 ሰዓት ጀምሮ ለሂስ የሚቀርበው መፅሀፍ የዶ/ር ምህረት ከበደ የመጀመሪያ ስራ የሆነው “የተቆለፈበት ቁልፍ” ሲሆን ለዚህ መፅሐፍ የውይይት መነሻ ሀሳብ የሚያቀርቡት በ“ፍቅር እስከ መቃብር” መፅሐፍ ላይ ለየት ያለ ትንታኔን “እውነትና ገሀድ” በተሰኘው መፅሀፋቸው ያስነበቡትና የስነ መለኮት ሊቁ ዶ/ር ዘካሪያ አምደ ብርሃን እንደሚሆኑ የዝግጅቱ አስተባባሪ አቶ በፍቅሩ
ዳኛቸው ገልፀዋል፡፡
    እነሆ መፅሀፍት መደብር፣ ሊትማን ቡክስና ክብሩ መፅሐፍት መደብር በመተባበር “ሀሳብን በሀሳብ መፈተን” በሚል መሪ ቃል በሚያዘጋጁት በዚህ አውደ ርዕይና የሂስ ጉባኤ፣ የመፅሀፍ እቁብን ጨምሮ ከ25 እስከ 50 በመቶ ቅናሽ የተደረገባቸውን መፅሐፍት መግዛትና በውይይቱ ላይ መሳተፍ የእውቀት አድማስን ማስፋት ነው ሲሉ አዘጋጆቹ ጋብዘዋል፡፡

Read 810 times