በወሩ መጨረሻ ባሉት ቅዳሜና እሁድ የሚካሄደው ትራኮን የመፅሀፍት አውደ ርዕይና የሂስ ጉባኤ፤ ዛሬና ነገ ጥቁር አንበሳ ፊት ለፊት በሚገኘው ትራኮን ታወር ይካሄዳል፡፡ ዛሬ ከቀኑ 8፡00 ሰዓት ጀምሮ ለሂስ የሚቀርበው መፅሀፍ የዶ/ር ምህረት ከበደ የመጀመሪያ ስራ የሆነው “የተቆለፈበት ቁልፍ” ሲሆን ለዚህ መፅሐፍ የውይይት መነሻ ሀሳብ የሚያቀርቡት በ“ፍቅር እስከ መቃብር” መፅሐፍ ላይ ለየት ያለ ትንታኔን “እውነትና ገሀድ” በተሰኘው መፅሀፋቸው ያስነበቡትና የስነ መለኮት ሊቁ ዶ/ር ዘካሪያ አምደ ብርሃን እንደሚሆኑ የዝግጅቱ አስተባባሪ አቶ በፍቅሩ
ዳኛቸው ገልፀዋል፡፡
እነሆ መፅሀፍት መደብር፣ ሊትማን ቡክስና ክብሩ መፅሐፍት መደብር በመተባበር “ሀሳብን በሀሳብ መፈተን” በሚል መሪ ቃል በሚያዘጋጁት በዚህ አውደ ርዕይና የሂስ ጉባኤ፣ የመፅሀፍ እቁብን ጨምሮ ከ25 እስከ 50 በመቶ ቅናሽ የተደረገባቸውን መፅሐፍት መግዛትና በውይይቱ ላይ መሳተፍ የእውቀት አድማስን ማስፋት ነው ሲሉ አዘጋጆቹ ጋብዘዋል፡፡
Published in
ኪነ-ጥበባዊ ዜና
Latest from Administrator
- የእስራኤል እና የኢራን ፍጥጫ
- Insights on Israel's Response: Interview with Mr. Tomer Bar-Lavi, Chargé d’Affaires at the Embassy of Israel to Ethiopia
- Barr, a vocal Trump critic, says he will ‘support the Republican ticket’ in November
- Iran president warns of ‘massive’ response if Israel launches ‘tiniest invasion’
- "አልሞቷል" ፊልም ዛሬ በዓለም ሲኒማ ይመረቃል