Monday, 03 April 2017 00:00

በጋና 208 የመንግስት መኪኖች በመጥፋታቸው አዲስ መኪና እንዳይገዛ ተወሰነ

Written by 
Rate this item
(1 Vote)

በጋና 208 የመንግስት መኪኖች የገቡበት ሳይታወቅ ጠፍተው መቅረታቸው መረጋገጡን ተከትሎ የአገሪቱ መንግስት ከአሁን በኋላ ለሚኒስቴር መሥሪያ ቤቶችና ለባለስልጣናት አገልግሎት የሚሰጡ አዳዲስ መኪኖች እንዳይገዙና አሮጌዎቹ ጥቅም መስጠታቸውን እንዲቀጥሉ መወሰኑን ቢቢሲ ዘግቧል፡፡
በሚሊዮኖች የሚቆጠር ዶላር የወጣባቸው ቪ ኤይት እና ፕራዶ የመሳሰሉ ውድ መኪኖች የውሃ ሽታ ሆነው መቅረታቸውን ተከትሎ የአገሪቱ ፕሬዚዳንት ናና አኩፎ አዶ ባስተላለፉት ውሳኔ፣ የህዝብ ሃብት እየባከነ በመሆኑ ከአሁን በኋላ ላልተወሰነ ጊዜ ለመንግስት መስሪያ ቤቶች አገልግሎት የሚሰጡ አዳዲስ መኪኖች አይገዙም ብለዋል፡፡
ስልጣኑን የለቀቀው መንግስት 707 የመንግስት መኪኖችን ለአዲሱ የአገሪቱ መንግስት ማስረከቡን ያስታወሰው ዘገባው፤ የአዶ መንግስት ስልጣን መያዙን ተከትሎ በተደረገ የሃብት ቆጠራ 234 መኪኖች መጥፋታቸው መረጋገጡንና የተወሰኑት በፍለጋ ሲገኙ የተቀሩት 208 መኪኖች ግን አሁንም ድረስ እምጥ ይግቡ ስምጥ ሳይታወቅ የውሃ ሽታ ሆነው መቅረታቸውን ጠቁሟል፡፡
የአገሪቱ መንግስት ፖሊስና ጉምሩክን ጨምሮ ከተለያዩ መስሪያ ቤቶች የተውጣጡ ግለሰቦችን በአባልነት የያዘ ልዩ ግብረ ሃይል አዋቅሮ የጠፉትን መኪኖች የማፈላለግና ከጉዳዩ ጋር ንክኪ ያላቸውን የቀድሞም ሆነ የአሁኑ የጋና መንግስት ባለስልጣናትን በቁጥጥር ስር አውሎ፣ ለህግ ለማቅረብ እየሰራ እንደሚገኝም ዘገባው ገልጧል፡፡

Read 1965 times