Print this page
Sunday, 26 March 2017 00:00

በ14ኛው ቅድሚያ ለሴቶች ሩጫ ‹‹የአዲዳስ ዲቨሎፕመንት ፕሮጀክት›› ወጣት አትሌቶች ማሸነፋቸው አስደንቋል

Written by 
Rate this item
(0 votes)

   በሚያዚያ ወር በጥቅል ‹‹ሶስታ ሃሴት›› የሚል ሰያሜ የተሰጣቸው 3 ተከታታይ ሩጫዎች ተዘጋጅተዋል

       በተባበሩት መንግስታት አብይ ስፖንሰርነት ‹‹ስለምትችል››  በሚል መርህ ከሳምንት በፊት ለ14ኛ ጊዜ የተካሄደው  የታላቁ ሩጫ በኢትዮጵያ ቅድሚያ ለሴቶች የ5 ኪ.ሜ የጎዳና ላይ ሩጫ ስኬታማ እንደነበር የውድድሩ አስተባባሪ  ዳግማዊት አማረ ለስፖርት አድማስ ገለፀች፡፡
11ሺ ተሳታፊዎች የነበሩት የጎዳና ላይ ሩጫው መነሻ እና መድረሻው በመደበኛው  አትላስ ሆቴል  መመለሱ ድምቀት ፈጥሯል ያለችው ዳግማዊት፤  ሩጫው ከመጀመሩ በፊት እና ካበቃ በኋላ የነበረው አጠቃላይ ድባብ ያማረ ነበር ብላለች፡፡ ውድድሩ ከመጀመሩ በፊት ከ150 ዓመታት በፊት ስለነበረች የኢትዮጵያ ጀግና ሴት የተሰራው የቃቄ ውርድዎት  ቲያትር አንድ የተቀነጨበ ትዕይነት ለእይታ መቅረቡ፤ በሴቶች እየተዘወተረ የመጣው ታዋቂው የዙምባ ዳንስ ደስ የሚል ትርኢቶችን በመፍጠር ውድድሩን ማሟሟቁ፤ እንዲሁም ስለምትችል የሚለው መርህን በማንገብ የሴቶችን ስኬትና ሚና ለማክበር የተደረጉት እንቅስቃሴዎች ስኬታማ እንደነበሩም አብራርታለች፡፡
በ5 ኪ.ሜትር የጎዳና ላይ ሩጫው በዋናው የአዋቂ አትሌቶች ውድድር አስደናቂ ውጤት የተመዘገበ ሲሆን በመሰረት ደፋር በባለቤቷ ቴድሮስ የሚንቀሳቀሰው የአዲዳስ  ዴፕሎፕመንት ፕሮጀክት ወጣት አትሌቶች ብዙም የውድድር ልምድ ባይኖራቸውም በአንደኛ እና  ሁለተኛ ደረጃ ውድድሩን በመጨረሳቸው ነበር፡፡ በ1ኛ ደረጃ የጨረሰችው የአዲዳስ ዴቨሎፕመንት አትሌት ደጊቱ አዝመራው ስትሆን ሌላዋ አጋሯ አበባ ተፈራ በሁለተኛ ደረጃ ተከትላ ገብታለች፡፡ ምህረት ተፈራ እና ብርሃን ምህረቱ ከሱር ኮንስትራክሽን 3ኛእና አራተኛደረጃ አግኝተዋል፡፡  በሌላ በኩል ከ35 ደቂቃ በታች 5 ኪሎሜትሩን ለሚጨርሱ  ስፖርተኞች ከሜዳልያ ሽልማት ባሻገር የአትሌት መሰረት ደፋር ፊርማ ያረፈበት 2000 ሰርተፍኬቶች ለሽልማት የቀረቡ ቢሆንም፤ በውድድሩ ላይ  ከ35 ደቂቃ በታች በመጨረስ የተሸለሙት 300 ብቻ ሆነዋል፡፡ በውድድሩ መነሻ ላይ በአንድ ጎዳና ላይ እጅብ ብሎ በመሮጥ የተፈጠረው  ግርግርና መጨናነቅ ብዙ ሴቶች ከ35 ደቂቃ በታች ውድድራቸውን እንዳይጨርሱ አድርጓቸዋል ብላለች፡፡ ዳግማዊት አማረ ከታላቁ ሩጫ በኢትዮጵያ  ፡፡ ከ30 በላይ ስፖርተኞችን ባሳተፈው የሴት ተምሳሌቶች  ውድድር የግሸን ፋርማሲ ባለቤት ወይዘሮ አማከለች ሉሉ ሲያሸነፉ በሁለተኛደረጃ የጨረሰችው ድምፃዊት ቤተልሄም ጌታሁን ወይም ቤቲ ጂ ነበረች፡፡ በአምባሳደርና የውጭ ዲፕሎማቶች ምድብ ደግሞ የስውድን አምባሳደር ባለቤት ሚስሪኮ ሜንሲያ  አሸንፈዋል፡፡    
ይህ በእንዲህ እንዳለ ታላቁ ሩጫ በኢትዮጵያ ከሚያዚያ 15  ጀምሮ  ባሉት ተከታታይ 3 እሁዶች የተለያዩ 3 ሩጫዎችን ማዘጋጀቱን ለስፖርት አድማ በላከው መግለጫ ያመለከተ ሲሆን ሶስቱ ተከታታይ ሩጫዎች በጥቅል ሶስታ ሃሴት (Triple Crown) የሚል ስያሜ ሰጥቷቸዋል፡፡ የመጀመርያው ሚያዚያ 15 የሚካሄደውና በአጠቃላይ 4000 ተሳታፊዎችን የሚያስተናግደው የሃዋሳው 2009 ሲሲኢሲሲ ሃዋሳ ግማሽ ማራቶን ሲሆን ይህ ሩጫ በውስጡ የ21 ኪ.ሜ.፤ የ7ኪ.ሜ እንዱሁም የህፃናት ሩጫ የሚያካትት ይሆናል፡፡  ሁለተኛው ውድድር
ታላቁ ሩጫ በኢትዮጵያ ከኢትዮጵያ ህክምና ባለሞያዎች ማህበር ጋር በመሆን የሚያዘጋጀው አመታዊው ኤማ ሩጫ  ሚያዚያ 22 ቀን ለ2ኛ ጊዜ ሲካሄድ  5000 ተሳታፊዎች ይኖሩታል፡፡
በመጨረሻም ሚያዚያ 29 ላይ የአውሮፓ ቀንን አስመልክቶ የሚዘጋጀው የአውሮፓ ቀን የህፃናት ሩጫ ሲሆን እድሜያቸው ከ3 አመት በላይ የሆኑ 3000 ህፃናት ወንዶችና ሴቶችን  የሚሳተፉበት ይሆናል፡፡

Read 1476 times
Administrator

Latest from Administrator