Monday, 13 March 2017 00:00

በምስራቅ አፍሪካ ከ17 ሚ. በላይ ሰዎች የርሃብ አደጋ ተጋርጦባቸዋል

Written by 
Rate this item
(1 Vote)

 የተባበሩት መንግስታት ድርጅት በምስራቅ አፍሪካ በሚገኙ ዘጠኝ አገራት በድምሩ ከ17 ሚሊዮን በላይ ሰዎች የርሃብ አደጋ እንደተጋረጠባቸው ማስታወቁን ቪኦኤ ዘግቧል፡፡ የተመድ ዋና ጸሃፊ አንቶኒዮ ጉቴሬዝ፤ ሶማሊያና
ደቡብ ሱዳንን ጨምሮ በአካባቢው በሚገኙ ዘጠኝ አገራት የርሃብ አደጋ ከተጋረጠባቸውና አስቸኳይ የሰብአዊ እርዳታ ከሚያስፈልጋቸው 17 ሚሊዮን ያህል ሰዎች መካከል 33 በመቶ ያህል የሚሆኑት ሶማሊያውያን መሆናቸውንና ከአገሪቱ ህዝብ ግማሽ ያህሉ የችግሩ ሰለባ መሆኑን ገልጸዋል፡፡ ባለፈው ማክሰኞ ሶማሊያን የጎበኙት ጉቴሬዝ፣ የዝናብ እጥረትና ግጭት በአገሪቱ የተከሰተውን ሰብአዊ ቀውስ እያባባሰው እንደሚገኝ በመጠቆም፤ አለማቀፉ ማህበረሰብ በሶማሊያና በሌሎች የምስራቅ አፍሪካ አገራት ለተከሰተው የርሃብ አደጋ አፋጣኝ ምላሽ እንዲሰጥ ጠይቀዋል፡፡

Read 1053 times