Saturday, 18 February 2017 13:56

ከ60 በላይ ሰዓሊያን የተሳተፉበት ‹‹አርት ፌር›› ተከፈተ

Written by 
Rate this item
(1 Vote)

    የኢትዮጵያ ቪዥዋል አርቲስቶች ማህበር ከ60 በላይ አባላት የተሳተፉበትና የተለያዩ የስዕል አሳሳል ዘይቤዎች የተንፀባረቁበት ‹‹አርትፌር” የተሰኘ የስዕል አውደ ርዕይ ባለፈው ረቡዕ በብሄራዊ ሙዚየም አቀረበ፡፡ የፊታችን ማክሰኞ ድረስ ለዕይታ ክፍት ሆኖ በሚቆየው በዚህ አውደ ርዕይ ላይ የተለያዩ የአሳሳል ቴክኒኮች የሚታዩባቸው እጅግ በርካታ ስዕሎች የቀረቡ በመሆኑ በስፋት ለማየትም ሆነ ለመግዛት በቂ አማራጮች እንዳሉት አዘጋጆቹ ገልጸዋል። እንደዚህ አይነት አርት ፌሮች በሌላው ዓለም የተለመዱና ለአድናቂዎች አማራጭ የሚቀርቡበት አሰራር ቢሆንም በአገራችን እንዲህ አይነት የስዕል አውደ ርዕዮች የተለመዱ እንዳልሆኑ የተናገሩት አዘጋጆቹ፤ በቀጣይ እንዲለመድ በተከታታይ ለማዘጋጀት ማቀዳቸውን ጠቁመዋል፡፡

Read 901 times