Saturday, 17 March 2012 10:21

ሕልምና ቅዠት ትናንትና ዛሬ” እየታየ ነው

Written by  መልካሙ ተክሌ (melkamutekele@gmail.com)
Rate this item
(0 votes)

በሰዓሊና ፎቶግራፈር አይዳ ሙሉነህ የተዘጋጁ 29 የፎቶግራፍ ስራዎች የቀረቡበት የፎቶግራፍ አውደርእይ ባለፈው ሰኞ ምሽት በአስኒ ጋለሪ ተከፈተ፡፡ የ”ዋሽንግተን ፖስት” ጋዜጣ ፎቶ ጋዜጠኛ የነበረችው አይዳ፤ ሥራዎቿን በሀገር ውስጥ  ስታቀርብ የመጀመሪያዋ ቢሆንም ካሁን በፊት በስፔን፣ በሰርቢያ፣ በማሊ፣ በግብጽ፣ በኩባ፣ በቻይና፣ በተባበሩት አረብ ኢምሬትስ፣ በአሜሪካና በቤልጂየም እንዳቀረበች ታውቋል፡፡

በአውደርእዩ ላይ የቀረቡት ፎቶግራፎች፤ ባህል፣ የማንነት ጥያቄና አብሮነት ላይ የሚያተኩሩ ሲሆን ፎቶግራፎቹ ከ2400 ብር እስከ 10,800 ብር የዋጋ ተመን ወጥቶላቸዋል፡፡ የዋጋውን መወደድ በተመለከተ ተመልካቾች ያነሱትን ጥያቄ ያቀረብንላት አርቲስቷ፤ “ሰው ፎቶግራፍ ማድነቅንና መግዛትን እንዲለምድ ዋጋው ዝቅ ብሎ ነው እንጂ በሌሎች ሀገራት የበለጠ ያወጣል” ብላለች፡፡ በ16 ዓመቷ ወደ ፎቶግራፍ ሙያ የገባችው አይዳ ሙሉነህ፤ በአውደ ርዕዩ ላይ የ12 ዓመት ሥራዎቿን ስብስብ አቅርባለች፡፡ ፎቶግራፈሯ በአሁኑ ወቅት በገብረክርስቶስ ደስታ ሥነጥበብ ቤተመዘክር በዳይሬክተርነት እየሰራች ትገኛለች፡፡

 

 

Read 1333 times Last modified on Saturday, 17 March 2012 10:22