Print this page
Sunday, 12 February 2017 00:00

የአ/አበባ ሀ/ስብከት: የተከፈለው 50ሺ ብር፥ “የፐርሰንት ውዝፍ እንጂ ጉቦ አይደለም፤” አለ

Written by 
Rate this item
(3 votes)

“ፐርሰንት ከደመወዝ ተቀንሶ አይከፈልም፤ አሠራሩም ሕጋዊ አይደለም” /ክፍለ ከተማው/
    በአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት፣ “የደብረ ተኣምራት ዳግማዊት ጻድቃኔ ማርያም ቤተ ክርስቲያን ካህናትና ሠራተኞች፤ ለተፈቀደላቸው የደመወዝ ጭማሪ ማጽደቂያ፣ ለሀገረ ስብከቱ ሓላፊዎች የተሰጠው ብር 50 ሺሕ ጉቦ እንዲመለስ ታዘዘ፤” በሚል ርእስ፣ አዲስ አድማስ ጋዜጣ ባለፈው ሳምንት ያወጣው ዘገባ፣ “ያልተጣራና መሠረተ ቢስ ነው” ሲሉ ሀገረ ስብከቱና የደብሩ ጽ/ቤት አስተባበሉ፡፡
ቤተ ክርስቲያኗ ካላት ከማንኛውም ገቢ ላይ ሃያ በመቶውን የሀገረ ስብከቱን ድርሻ እንድትከፍል በቃለ ዐዋዲው መደንገጉን በማስተባበያቸው አስታውሰው፤ በዘገባው የተጠቀሰውና ከደብሩ ጽ/ቤት ወጣ የተባለው 50ሺ ብርም፣ በወቅቱ ያልተከፈለ የደብሩ የሃያ ፐርሰንት ውዝፍ ሒሳብ መሆኑን አስረድቷል፡፡ ይህም፣ ሀገረ ስብከቱን ወክሎ በሚሠራው በኮልፌ ቀራንዮ ክፍለ ከተማ ቤተ ክህነት ጽ/ቤት ስም በኢትዮጵያ ንግድ ባንክ በተከፈተው ተንቀሳቃሽ ሒሳብ ገቢ መደረጉን በመጥቀስ ደረሰኙን በአስረጅነት አቅርቧል፡፡ “ወደ ተቋሙ ባንክ የገባውን ገንዘብ ለግለሰቦች እንደተሰጠ አስመስሎ መዘገቡ ሚዛናዊነት የጎደለው ነው፤” ሲልም ዘገባውን ተቃውሟል፡፡ የኮልፌ ቀራንዮ ክፍለ ከተማ ቤተ ክህነት ሥራ አስኪያጅ፣ መጋቤ ሠናያት የቻለው ለማ በበኩላቸው፤ “የደብሩ የሃያ በመቶ ውዝፍ ዕዳ መከፈል ያለበት ከደብሩ ገቢ እንጂ ከሠራተኞች ደመወዝ ተቀንሶ መሆን የለበትም፤ የሁለት ወሩ የደመወዝ ጭማሪም የተቀነሰው፣ የጽ/ቤቱ ሓላፊዎች በራሳቸው ወስነው እንጂ፣ የሚመለከተው ሰበካ ጉባኤ በተገኘበት እንዳልሆነ ጽ/ቤታቸው ባደረገው የሰነድና የገጽ ለገጽ ማጣራት ማረጋገጡን ገልጸዋል፡፡ ገቢ ተደርጓል ስለተባለው 50ሺ ብር የተጠየቁት ሥራ አስኪያጁ፣ “የክፍለ ከተማው ጥያቄ የ50ሺሕ ብር አከፋፈል ሒደት አይደለም፤ ከግለሰቦች ላይ የተቀነሰው የገንዘብ አከፋፈል ሒደትና አሠራር ትክክል አይደለም፤ ፍትሐዊ አይደለም፤ ነው፤” በማለት ከደመወዝ ጭማሪው ጋር ግንኙነት እንደሌለው አስረድተዋል፡፡


Read 4326 times
Administrator

Latest from Administrator