Sunday, 05 February 2017 00:00

አገር የሚያድገው በቢዝነስ አድሚኒስትሬሽን ነው

Written by 
Rate this item
(4 votes)

     ‹‹ቢዝነስ አድሚኒስትሬሽን ማለት ሐሳብንና ገንዘብን አቀናጅቶ ሥራ መፍጠር ነው፡፡ ሰዎች እዚህ ተምረው ወጥተው እንዴት የራሳቸውን ሥራ መፍጠር እንደሚችሉ ነው የምናስተምረው፡፡ ሐሳብና ገንዘብ እንዴት እንደሚቀናጁ መንገድ እናሳያለን፡፡ ከፊዚቢሊቲ ጥናት አንስቶ ማርኬቲንግና ፋይናንሻል ስትራቴጂ እንዴት እንደሚቀረጽ እናስተምራለን፡፡ ምክንያቱም ያለ ፋይናንስ (ገንዘብ) ሐሳብ ብቻውን ውጤታማ አይሆንም፡፡ ድሮ በአገራችን ገንዘብ ያለው ሰው ነጋዴ፣ ነጋድራስ ይሆን ነበር፡፡ አሁን ግን ሁኔታዎች ተለውጠዋል፡፡ ሐሳብ ሆኗል ገንዘብ፡፡ እነ ጎግል፣ እነ ፌስቡክ የሐሳብ ውጤቶች ናቸው፡፡ ሐሳብ ነው ብር እየሆነ የመጣው፡፡ እኛ የምናስተምረው ሐሳብን ከገንዘብ ጋር አቀናጅቶ እንዴት ወደ ሥራ መተርጎም እንደሚቻል ነው፡፡‹‹በዚች አገር አንድ ሰው ሐሳብ ይዞ ሲነሳ፣ ብዙም ተቀባይነት የለውም፡፡ ባንኮች እንዴት ገንዘብ ሊያበድሩት እንደሚችሉ፣ ብር ያላቸው ሰዎች እንዴት ገንዘባቸውን ሊሰጡት እንደሚችሉ እንዲቀምር ነው የምናስተምረው፡፡ አገልግሎት ሰጪዎች ደግሞ እንዴት ሊጠቀሙ እንደሚችሉ፣ ከአራትና አምስት ዓመት ገቢያቸው ጋር እንዲያስተያዩት፤ እንዴት የበለጠ ገቢ ማግኘት እንደሚችሉ፣ ገንዘባቸውን ባንክ ከሚያስቀምጡ ኢንቨስት ቢያደርጉ የተሻለ ገቢ እንደሚያገኙ ማሳመን መቻልን ነው የምናስተምረው ‹‹ከአንድ ቢዝነስ ወጥቶ እንዴት ሌላ የተሻለ ቢዝነስ መጀመር እንዳለበትም እናስተምራለን፡፡ ቀደም ሲል አያቱ ወይም አባቱ ቤንዚን ማደያ ካላቸው ልጃቸውም ቤንዚን ማደያ ነው የሚኖረው፡፡አሁን ግን ያ አይደለም ዘመናዊ ቢዝነስ፡፡ ቢዝነሱ በፊት ከነበረበት አድጎ ነው መገኘት ያለበት፤ ወደ ፈጠራ ነው መሸጋገር ያለበት፡፡ የቢዝነስ ሞዴል አስተዳደር ትምህርት ይህ ነው›› ብለዋል የዌስተርን ዩኒቨርሲቲ ኮሌጅ ፕሬዚዳንትና የኤምቢ ኤ ፕሮግራም ሥራ አስፈጻሚ ዋና ዳይሬክተር አቶ አቤቱ መላኩ፡፡ ከተመሰረተ አንድ መቶ ዓመት ሊሆነው ሁለት ዓመት ብቻ የቀረው የሊንከን ዩኒቨርሲቲ አካል የሆነው ዌስተርን ዩኒቨርስቲ ኮሌጅ ባለፈው ሳምንት በሁለተኛ ዲግሪ በኤምቢኤ (Masters of Business Administration) ለ6ኛ ዙር፣ በቢዝነስ አድሚኒስትሬሽን (ቢኤ) ዲግሪ ለመጀመሪያ ጊዜ ያስተማራቸውን ተማሪዎች ባለፈው ሳምንት እዚህ አዲስ አበባ በአፍሪካ ኢኮኖሚክ ኮሚሽን አዳራሽ በድምቀት አስመርቋል፡፡ ለመሆኑ ዌስተርን ዩኒቨርሲቲ ኮሌጅ እንዴት በአገራችን (Masters of Business Administration (ኤምቢኤ) ትምህርት መጀመር ቻለ? መቼ? መልሱን አቶ አቤቱ ይነግሩናል፡፡ ከተመሰረተ 98 ዓመታትን ያስቆጠረው፣ በአሜሪካ፣ ካሊፎርኒያ ግዛት ኦክላንድ ከተማ የሚገኘው ሊንከን ዩኒቨርሲቲ በአራት ወይም በአምስት
አገሮች በኤክስቴንሽን ያስተምራል፡፡ የአፍሪካ ተወካይ ናይጀሪያ ነበረች፡፡ ይህ ካምፓስ በፀጥታ ችግር መዘጋቱን አቶ አቤቱ በማስታወቂያ ሰሙ፡፡ እንዴት አፍሪካን የሚያህል አህጉር ያለ ሊንከን ዩኒቨርሲቲ ተወካይ ይቀራል? በማለት ጠየቁ እኛ ለደህንነታችን ነው ቅድሚያ
የምንሰጠው ተባሉ፡፡ በዚህ ጊዜ ኢትዮጵያ አፍሪካን እንድትወክል ተመኙና ኢትዮጵያስ? በማለት ጠየቁ በኢትዮጵያ ሰላም አለ? ኢትዮጵያ (አዲስ አበባ) የአፍሪካ ኢኮኖሚክ ኮሚሽን፣ በርካታ ዓለም አቀፍና አኅጉር አቀፍ ድርጅቶች ያሉባት፣ ፈረንጆች በእኩለ ሌሊት የሚንሸራሸሩባት ናት በማለት መለሱ፡፡ “ለምን ፕሮፖዛል ጽፈህ ለባለ አደራ ቦርድ አቅርበህ አትሞክርም?” አሏቸው፡፡ ፕሮፖዛል ፅፈው አስገቡና ሰዎችም ረድተዋቸው ተቀባየነት አገኙ፡፡ የባለ አደራ ቦርዱ ሊቀ መንበር ግን ጥርጣሬ ገባቸው፡፡ ‹‹ይህ ሰው የተማረው ስለ ቢዝነስ ነው፡፡ የአካዳሚክ እውቀት የለውም፡፡ ታዲያ እንዴት ዩኒቨርሲቲውን መምራት ይችላል?” ሲሉ ጠየቁ፡፡ ቀደም ሲል አቶ አቤቱ ብሉናይል ኢንተርፕራይዝ  ኩባንያ አቋቁመው፣ ለመጀመሪያ ጊዜ አምቦ ውሃንና በደሌ ቢራን ወደ አሜሪካ ወስደው ለ5 ዓመት የሸጡና ያስተዋወቁ ሰው
ናቸው፡፡ እዚህ አገር ቤት በተፈጠረ ችግር ተቋረጠ እንጂ አምቦ ውሃው በአሜሪካ ገበያ ጥሩ ተቀባይነት አግኝቶ ነበር፡፡  ለባለአደራ ቦርዱ ሊቀመንበር ጥያቄ፣ የሊንከን ዩኒቨርሲቲ ፕሬዚዳንት ሲመልሱ፣ ‹‹ከአፍሪካ (ኢትዮጵያ) ውሃ አምጥቶ በአሜሪካ ገበያ መሸጥ ከቻለ፣ ይህንን
ዩኒቨርሲቲ አገር ቤት ወስዶ እንዴት ነው መምራት የሚያቅተው?” በማለት ተሟገቱላቸው፡፡ በዚህ ዓይነት በሊንከን ዩኒቨርሲቲ ተወክለው ወደ ኢትዮጵያ ተላኩ፡፡
ሊንከን ዩኒቨርሲቲ… እዚህ (ኢትዮጵያ) ሲመጣ ድንበር ተሻጋሪ ስለሚባል ትምህርት ግልጽ መመሪያ አልነበረም፡፡ ‹‹ጥርጣሬውም ስለነበር ሊፈቅዱልኝ አልፈለጉም ነበር፡፡ ሦስት ወር ሙሉ ከወዲያ ወዲህ በመመላለስ ጫማዬን ጨርሼ ምንም ውጤት ስላላገኘሁ፣ ከፍተኛ ፍርሃትና
ስጋት ገብቶኝ ነበር›› ይላሉ አቶ አቤቱ ሊንከን ዩኒቨርሲቲን በኢትዮጵያ ለማቋቋም ገጥሟቸው የነበረውን ችግር ሲያስታውሱ፡፡ በመጨረሻም  ተስፋ ቆርጠው ወደ አሜሪካ ለመመለስ ሲነሱ፣ ቀደም ሲል ያውቋቸው የነበሩትን ወዳጃቸውን፤ ‹‹ሰላም ሁን›› ለማለት ቢሮአቸው
ደወሉላቸው፡፡ ወዳጃቸውም ‹መቼ መጣህ?›› በማለት ጠየቁ፡፡ አቶ አቤቱ ‹‹አይ፤ ሳላይህ ብሄድ ውቃቢህ ያየኛል ብዬ ነው የደወልኩት እንጂ መሄዴ ነው›› አሉ፡፡፡ ወዳጃቸውም ‹‹መቼ መጣህ›› አሉ፡፡ ‹‹ለዚህ ጉዳይ ነበር የመጣሁት፡፡ አሁን ስላልተሳካልኝ ተስፋ ቆርጨ መመለሴ ነው››
በማለት መለሱ፡፡ ‹‹ስልኩን ዝጋው፤ መጣሁ›› ብለው፤ አቶ አቤቱ ወደ ነበሩበት ሄደው በመኪና ወደ ቢሯቸው ወሰዷቸውቢሮ እንደደረሱ ለምን ወደ ኢትዮጵያ እንደመጡ፤ ያደረጉትን ጥረት፣ አልሳካ ቢላቸው ተስፋ ቆርጠው ለመመለስ እንደወሰኑ በዝርዝር
አጫወቷቸው፡፡ ወዳጃቸው በሰሙት ነገር በጣም ተገረሙ፡፡ በጠቅላይ ሚኒስትሩ ቢሮ የሚያውቋቸው ሰዎች ስለነበሩም እነሱን በስልክ አግኝተው ስለጉዳዩ አጫወቷቸውና፤ ‹‹እንዲህ ያለ ነገር እንዴት ይታለፋል? ያገር ጉዳይ’ኮ ነው›› በማለት ፋክስ አደረጉላቸው፡፡ ከዚያም አሪጂናል ዶክመንቶችን አገላብጠው ተመለከቱ፡፡ ‹‹ ይህን ይዘህ ማን ጋር ሞከርክ?›› በማለት ጠየቋቸውየ‹‹እገሌ የሚባል ያልሞከርኩበት ባለሥልጣን የለም፡፡ በማለት መለሱ፡፡ ‹‹ለምን አንድ ሦስት ቀን አትቆይም?›› አላቸው፡፡ አቶ አቤቱም፤ ‹‹ኢትዮጵያ ውስጥ ጉዳይ አያልቅም፡፡ ስለዚህ ተመልሼ መስራት አለብኝ፡፡ በጊዜ አልቀልድም፣ ስለ ጊዜ አጠቃቀም ነው የተማርኩት›› አላቸው  ሰዎቹም፤ ‹‹ግድ የለም፤ ተስፋ አትቁረጥ፤ እኛም እንረዳሃለን››አሏቸው፡፡
በዚህ ዓይነት ከሚመለከታቸው ቢሮዎች ጋር ግንኙነት መፍጠር ተጀምሮ ፈቃድ ተሰጣቸው፡፡ ፈቃዱን ሲያገኙም ብቻቸውን እንዲሠሩ ሳይሆን፣ አስተማማኝነቱ ከተረጋገጠ ተቋም ጋር ተዳብለው እንዲሰሩ ከኒው ጀኔሬሽን ዩነቨርሰቲ ኮሌጅ ጋር ተዳብለው በ2010 መሥራት ጀመሩ፡፡ ለአንድ ዓመት ከሰሩ በኋላ በተለያዩ ምክንያቶች ከኮሌጁ ጋር ተዳብሎ መስራቱን አስተዳደሩም ሆነ ተማሪዎች ስላልወደዱት፣ እንደገና
አመልክተው ፈቃድ ስላገኙ ነፃ ሆነው በራሳቸው መስራት መጀመራቸውን አቶ አቤቱ አስረድተዋል፡፡
 ዩኒቨርሲቲውን ለመክፈት ግን በጣም ፈታኝ ችግሮች ገጥሟቸው እንደነበር አቶ አቤቱ ይናገራሉ፡፡ ተስፋ ቆርጠው ሊመለሱ ሲነሱ፣ ጠቅላይ ሚኒስትሩ ጽ/ቤት በነበሩ ሰዎች ድጋፍ አግኝቶ (እ.ኤ.አ)፣ በ2010 ከኒውጀኔሬሽን ዩኒቨርሲቲ ጋር ተዳብሎ እንዲሠራ ፈቃድ እንደተሰጠው ገልጸዋል፡፡ሊንከን ዩኒቨርሲቲ ኮሌጅ የሚያስተምረው ስለቢዝነስ ነው፡፡ ዘመናዊ የቢዝነስ ጥበብ አስተምሮ በማስተርስ (ሁለተኛ) ዲግሪ ያስመርቃል፡፡ ዘንድሮ ግን ለማስተርስ ፕሮግራም ሥልጠና ብቁ የሆኑና ተገቢውን መመዘኛ የሚያሟሉ ተማሪዎችን ለመመልመል ያስችለው ዘንድ ለመጀመሪያ ጊዜ በቢዝነስ አድሚኒስትሬሽን አስተምሮ 18 ተማሪዎችን በመጀመሪያ ዲግሪ አስመርቋል፡፡ዩኒቨርሲቲ ኮሌጁ፣ በዲያግኖስቲክ ኢ-ሜጂንግ (ስካኒንግ፣ ሲኖግራፊ፣) ስፔሻላይዝድ ያደረገ ስለሆነ በሚቀጥለው ዓመት በዚህ እውቀት
አስተምሮ በመጀመሪያ ዲግሪ ለማስመረቅ አቅዷል፡፡ ነገር ግን አንድ ችግር አለበት፡፡ ይኼውም ተማሪዎች ወጥተው ልምምድ የሚያደርጉበት ሆስፒታል ያስፈልጋል ሁለተኛ፣ ለሆስፒታሉ የሚያገለግሉ መሳሪያዎች መግባት አለባቸው፡፡ መሳሪያዎቹን ለማስገባት የጉምሩክ ፈቃድ
ይፈልጋል፡፡ ፈቃዱን ለማግኘት ደግሞ ዕቃዎች መሟላት አለባቸው የሚል ችግር ቢያጋጥማቸውም ይፈታል የሚል ተስፋ እንዳላቸው ዳይሬክተሩ ገልጸዋል፡፡ የእኛ ዩኒቨርሲቲ ልዩ ኳሊቲው (ጥራቱ) የትምህርት አሰጣጡ ካሪኩሌም የሚቀረፀው በ1919 ዓ.ም በተመሠረተውና ዕድሜ ጠገብ በሆነው
ሊንከን ዩኒቨርሲቲ ነው ያሉት አቶ አቤቱ፣ ከሚያስተምራቸው 11 ኮርሶች ስምንቱን መምህራን ከአሜሪካ ሊንከን ዩኒቨርሲቲ መጥተው እንደሚያስተምሩ፣ ሦስት ኮርሶች ብቻ እዚህ ባሉ መምህራን እንደሚሰጥ ገልጸዋል፡፡ እኛ የምንደራደረው በጥራትና ጥራት ብቻ ነው፡፡
የምናስተምራቸውን ጥቂት ሰዎች በጥራት አውጥተን ተወዳዳሪ እንዲሆኑ እናደርጋለን ዩኒቨርሲቲው በትምህርት መረጃ መጻሕፍት የተሟላ መሆኑን አቶአቤቱ ይናገራሉ፡፡ ‹‹ኢትዮጵያ ውስጥ ኤሌክትሮኒክስ ቤተ መጽሐፍት የተጀመረው በእኛ ዩኒቨርሲቲን ነው፡፡ ዳታ ቤዙ አሜሪካ ሆኖ ተማሪዎች እዚህ ተቀምጠው የሊንከን ዩኒቨርሲቲ ቤተ መጻሕፍት ነው የሚጠቀሙት፡፡ መጽሔትና ጋዜጦችን  ጨምሮ የበርክሌይ ዩኒቨርሲቲ ቤተ መጻሕፍት መጠቀም ይችላሉ፡፡ ከአሜሪካ የሚመጡ መምህራን በኢንተርኔት ከራሳቸው መጻሕፍት ነው የሚያስተምሩት፡፡ የእኛ
ዩኒቨርሲቲ መምህራን ለየት ያሉ ናቸው፡፡ ትምህርታቸው እንደዚህ አገር መምህራን በንድፈ ሐሳብ (ቲዮሪ) ላይ ብቻ የተመሠረተ አይደለም፡፡ ቢዝነስ ላይ ያሉና ሕይወታቸውን እየኖሩበት ያለውን ልምድ ነው የሚያስተምሩት፡፡ ለምሳሌ በምረቃው ላይ የተገኙት የባለአደራ ቦርዱ
ሊቀመንበር የህክምና ዶክተር (አንኮሎጂ- የካንሰር ስፔሻሊስት) ናቸው። ነገር ግን እዚህ ሲመጡ የሚያስተምሩት የ200 ሆስፒታሎች ኃላፊ ስለሆኑ ሊደርሺፕና ኮሙኒኬሽን ነው››  በማለት አብራርተዋል፡፡  ለአንድ አገር እድገትና ለውጥ ትምህርት እጅግ አስፈላጊ ነው፡፡ ነገር ግን ቁጥር ሳይሆን በጥራት ሲሰጥ ነው የተፈለገው ራዕይ እውን የሚሆነው ይላሉ - አቶ አቤቱ፡፡ ‹‹ የእኛ የወደፊት ዕቅድ ከመዋዕለ ህፃናት እስከ ሁለተኛ ዲግሪና ዶክትሬት ድረስ ከስር መሰረቱ ኮትኩቶ ማውጣት ነው፡፡
የእኛ ዕቅድ እንደ ሀርቫርድና እንደ ስታንፎርድ ዩኒቨርሲቲዎች ተማሪዎችን ከሥር ከመሰረቱ ኮትኩቶ ማውጣት ነው፡፡ ፐሮፖዛል አስገብተን የመሬት ጥያቄም አቅርበናል” ሲሉ ተናግረዋል፡፡በምረቃው ሥነ-ሥርዓት ላይ ከአሜሪካ- ሳንፍራንስኪስኮ ከሪችሞንድ ከተማ ሳንቴ የተባለ ሬስቶራንት ባለቤት ወ/ሮ መንበረ አክሊሉ በሊንከን ዩኒቨርሲቲ ኮሌጅ ኃላፊዎች ጋባዥነት ተገኝታ፣ የስኬት ታሪኳን ለተመራቂዎች ተናግራለች፡፡ በሌላ በኩል ሊንከን ዩኒቨርሲቲ ኮሌጅ ለመጀመሪያ ጊዜ በተለያዩ የቢዝነስ ዘርፎች ተሰማርተው ለአገር ኢኮኖሚ ዕድገት የላቀ አስተዋጽኦ ላደረጉት ለአቶ ብዙአየሁ ታደለ፣ የክብር ዶክትሬት ዲግሪ ሰጥቷል፡፡ሊንከን ዩኒቨርሲቲ ባሳለፋቸው ስድስት ዓመታት ብዙ ችግሮችን ቢያጋጥሙትም ዋናው ችግር ቢሮ ክራሲው መሆኑን ፕሬዚዳንቱ ገልጸዋል፡፡ ‹‹የከፍተኛ ትምህርት ጥራትና ብቃት ኤጀንሲ የሚባለው ድርጅት ገምጋሚ ብቻ ሳይሆን ተገምጋሚም ነው ለእኔ፡፡ በድንገት መጥተው የሚጠይቁት የዛሬ 30 እና 40 ዓመት የሚሠራበትን ነገር ነው፡፡ ለምሳሌ በዋይ ፋይ ዘመን ላይ እያለን፣ የግድ ገመድ ያለው ኮምፒዩተር ማሳየት የለብንም፡፡ ኔትወርኩ የታለ? በማለት ይጠይቃሉ›› ብለዋል፡፡ ዩኒቨርሲቲው የሚጠይቀው ክፍያ ወደድ እንደሚል አቶ አቤቱ ያምናሉ፡፡ ‹‹እኛ የምናስተምረው የርቀት (non-distance) አይደለም፡፡ በክፍል ውስጥ ከተማሪዎች ጋር ፊት ለፊት (non-Distance) ነው፡፡ ስለዚህ መምህራኑ ከአሜሪካ ሲመጡ የአውሮፕላን ይከፈላል፣ ክፍል ገብተው የሚያስተምሩበት የአበል ብቻ 1400-1500 ብር ይከፈላቸዋል፡፡ ሌላው ክፍያውን የሚያንረው የማስተማሪያ ሕንፃው ኪራይ ነው፡፡ ለሕንፃው ኪራይ የሚከፈለው 85 ሺ ብር ቢቀር፣ በእርግጠኝነት የተማሪዎች ክፍያ ይቀንሳል፡፡ ከዚህም በተጨማሪ የአዲስ አበበ ከተማ አስተዳደሩ ይህን ችግር ተግዝቦ ሕንፃ መሥሪያ ቦታ ቢሰጠን፣ ወደፊት የተማሪዎች ቁጥር ስለሚጨምር፣ የትምህርት ክፍያውም ይቀንሳል›› በማለት አስረድተዋል፡፡

Read 3134 times