ለምርምራቸው የ600 ሺህ ዶላር የገንዘብ ድጋፍ አግኝተዋል
አሜሪካ በሚገኘው ኒው ሜክሲኮ ዩኒቨርሲቲ የኬሚስትሪና ኬሚካል ባዮሎጂ የትምህርት ክፍል መምህር የሆኑት ኢትዮጵያዊው ረዳት ፕሮፌሰር ተረፈ ሃብተየስ፣ የአገሪቱ ብሄራዊ የሳይንስ ፋውንዴሽን፣ በምርምር ዘርፍ የላቀ ውጤት ላስመዘገቡ ምሁራን የሚሰጠው “የታላቁ የፋካልቲ ኧርሊ ካሪየር ዲቨሎፕመንት አዋርድ” አሸናፊ መሆናቸው ተዘግቧል፡፡
ረዳት ፕሮፌሰር ተረፈ ሃብተየስ፤ በዩኒቨርሲቲው የላቀ ቴክኖሎጂ ቁሳቁስ ምርምር ማዕከል፣ ከግብረ አበሮቻቸው ጋር ለሚያከናውኑትና አምስት አመታትን ለሚወስደው የምርምር ፕሮጀክት ማስፈጸሚያ፣ የ600 ሺህ ዶላር የገንዘብ ድጋፍ ማግኘታቸውን ዩኒቨርሲቲው በሳምንቱ መጀመሪያ በድረገጹ ላይ ባወጣው መረጃ ጠቁሟል፡፡ ረዳት ፕሮፌሰሩ በምርምር ፕሮጀክቱ፣ እጅግ ጥቃቅን የሆኑ ረቂቅ አካላትን ለማየት የሚያስችል በአይነቱ የተለየ ማይክሮስኮፕ ለመፍጠር እንደሚሰሩ የጠቆመው መረጃው፤ ማይክሮስኮፑ ለቀጣይ ምርምሮች ከፍተኛ አስተዋጽኦ እንደሚያበረክትም አመልክቷል፡፡
የመጀመሪያና የሁለተኛ ዲግሪያቸውን በኬሚስትሪ ከአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ የተቀበሉት እኒሁ ኢትዮጵያዊ ምሁር፣ የፒኤችዲ ትምህርታቸውን በዩኒቨርሲቲ ኦፍ አሪዞና ያጠናቀቁ ሲሆን በዩኒቨርሲቲ ኦፍ ካሊፎርኒያ የፖስት ዶክቶራል ምርምራቸውን እንደሰሩ ለማወቅ ተችሏል፡፡ እ.ኤ.አ ከ2012 አንስቶ በታዋቂው ኒው ሜክሲኮ ዩኒቨርሲቲ በማስተማር ላይ እንደሚገኙም ተጠቁሟል፡፡
Published in
ህብረተሰብ
Latest from Administrator
- የእስራኤል እና የኢራን ፍጥጫ
- Insights on Israel's Response: Interview with Mr. Tomer Bar-Lavi, Chargé d’Affaires at the Embassy of Israel to Ethiopia
- Barr, a vocal Trump critic, says he will ‘support the Republican ticket’ in November
- Iran president warns of ‘massive’ response if Israel launches ‘tiniest invasion’
- "አልሞቷል" ፊልም ዛሬ በዓለም ሲኒማ ይመረቃል