በሌላ በኩል በዋልት ዲዝኒ ፒክቸርስ የተሰራው “ጆን ካርተር” የተባለ የሳይንሳዊ ልቦለድ ፊልም ከፍተኛ በጀት ወጥቶበት ቢሰራም ለኪሳራ ሊዳረግ ይችላል ተባለ፡፡ ፊልሙን ለመስራት እና ለማስተዋወቅ 350 ሚሊዮን ዶላር ወጭ መደረጉን ያመለከተው “ዘ ሆሊውድ ሪፖርተር”፤ የመጀመርያ ሳምንት ገቢው 100 ሚሊዮን ዶላር እንደነበር ዘግቧል፡፡ ፊልሙ የሰው ልጅ ማርስን ለመጀመርያ ጊዜ ሲረግጥ በፕላኔቷ ፍጡራን የሚደርስበትን ጥቃት የሚያሳይ እንደሆነ ታውቋል፡፡ በከፍተኛ በጀትና የጥራት ደረጃ የተሰራው “ጆን ካርተር”፤ ከ600 ሚሊዮን ዶላር በላይ ገቢ ያስገባል ተብሎ ተጠብቆ ነበር፡፡ ፊልሙ ሰሞኑን ለእይታ ሲበቃ ግን የተጠበቀውን ገቢ ሳያስገኝ በመቅረቱ ምናልባትም እስከ 165 ሚሊዮን ዶላር ሊያከስር ይችላል ብለዋል - የዎልስትሪት ኢኮኖሚስቶች፡፡