Saturday, 14 January 2017 16:14

“ESOG… 25ኛ አመት...”

Written by 
Rate this item
(1 Vote)

ጥር 25-27 የኢትዮያ የጽንስና ማህጸን ሐኪሞች ማህበር 25ኛ አመት የብር ኢዮቤልዩ፣
ጥር 25-27 የኢትዮያ የጽንስና ማህጸን ሐኪሞች ማህበር ESOG ›መታዊ ጉባኤ፣
ጥር 25-27 የአፍሪካ የጽንስና ማህጸን ሐኪሞች ማህበር ፌደሬሽን 2ኛ ጉባኤ ይካሄዳል።
የኢትዮጵያ የጽንስና ማህጸን ሐኪሞች ማህበር ከተቋቋመ 25 አመት ሞላው። ጉባኤው የሚከና ወነው የኢትዮጵያ ፌደራላዊ ዲሞክራሲያዊ ጤና ጥበቃ ሚኒስር፣ የአለም የጽንስና ማህጸን ሐኪሞች ፌደሬሽን እና የአፍሪካ የጽንስና ማህጸን ሐኪሞች ማህበር ፌደሬሽን በተባባሪነት በማ ዘጋጀት ነው። የኢትዮያ የጽንስና ማህጸን ሐኪሞች ማህበር ባለፉት 25 አመታት የሰራቸው ስራዎች ምን እንደሚመስሉ ዶ/ር ደረጀ ንጉሴ የማህበሩ ፕሬዝዳንት እንደሚከተለው አብራርተዋል።
በስነተዋልዶ ጤና የሚያገለግሉ ሙያዊ ትንተናዎችን ለማቅረብ በአገር ደረጃ በሚዋቀሩ የተለያዩ ኮሚዎች ውስጥ በመሳተፍ ሁነኛ የሆነ አስተዋጽኦ አድርጎአል።
ባለፉት 25 አመታት ከ20 በላይ የሆኑ እጅግ ተጠቃሽ የሆኑ ፕሮጀክቶችን ከተለያዩ አጋር ድርጅቶች ጋር በመተባበር አከናውኖአል።
ኤችአይቪ ከእናት ወደልጅ እንዳይተላለፍ ለመግታት ደረጃውን የጠበቀ ሕክምና እንዲሰጥ ከማድረግ አኩዋያ ወደ 70የሚሆኑ የህክምና ድርጅቶች ውስጥ የሚገኙ ባለሙያዎችን ማሰልጠንና በተጨማሪም ክትትል በማድረግ የበኩሉን ሚና ተጫውቶአል።
በመካከለኛ ደረጃ የሚገኙ የጤና ባለሙያዎችን በማዋለድ ተግባር ላይ የተሸለ ክህሎት ኖሮአቸው በተለይም በኦፕራሲዮን መውለድ የሚያስፈልጋቸውን እናቶች ከመደገፍ አኩዋያ ቁጥራቸው ወደ 47 ለሚሆኑ የጤና ባለሙያዎች ስልጠና ሰጥቶአል። ይህ ስልጠና እስከ 6 ወር የደረሰ ተከታታይ ስልጠና ሲሆን በተለይም እስፔሻሊስት ሐኪሞች በማይገኙበት ቦታ ለወላድ እናቶች ባለሙያው አስፈላጊውን እገዛ ሊያደርግ የሚችልበት ስራ ተሰርቶአል። በዚህም ፕሮጀክት እስከ መቶ ሺህ እናቶች ተጠቃሚ ሆነዋል።
በወሲባዊ ጥቃት እና ትንኮሳ ዙሪያ በተለይም ሴቶች ጥቃቱ ከደረሰባቸው በሁዋላ ተገቢውን ሕክምና እንዲያገኙ እና ክትትል እንዲደረግላቸው የኢትዮጵያ የጽንስና ማህጸን ሐኪሞች ማህበር ከአጋር ድርጅቶች ጋር በመሆን በአዲስ አበባና በተለያዩ መስተዳድሮች ዋና ዋና ከተሞች ውስጥ 6 ሞዴል ክሊኒኮችን በመመስረት ደረጃውን የጠበቀ ሕክምናና እንክብካቤ እንዲያገኙ አድርጎአል።
በማደግ ላይ ባሉ ክልሎችና በአርብቶ አደሮች አካባቢ የማህረሰቡን የስነተዋልዶ እውቀ ትና ግንዛቤ ከማሳደግ አኩዋያ የሚሰሩ ስራዎች ያሉ ሲሆን ከዚህ በተጨማሪም ሙያተ ኞች እርህራሔንና ተገቢ የሆነን የህክምና እርዳታ ለተገልጋዩ ለማዳረስ የሚችሉበትን ስልጠና ማህበሩ በመስጠት ላይ ነው።
ማህበሩ ከ20 በላይ የሚሆኑ ሙያነክ መመሪያዎችን በማዘጋጀት ደረጃውን የጠበቀ ግልጋሎት ለማህበረሰቡ እንዲሰጥ ሲያደርግ ቆይቶአል።
 ስለዚህም በአጠቃላይ ላለፉት 25 አመታት ዘርፈ ብዙ የሆኑ በስነተዋልዶ ጤና ዙሪያ የተሰሩ ስራዎችን ማህበሩ አከናውኖአል። ከዚህም በተረፈ በአገር ውስጥ ከሚካሄዱት እንቅስ ቃሴዎች ባሻገር በምስራቅ ፣በመካከለኛውና በደቡብ አፍሪካ ሐገራት በተመሰረተው የማህጸንና ጽንስ ሕክምና ማህበር ፌደሬሽን ተሳትፎ ከማድረግም ባሻገር ማህበሩን የመምራት ኃላፊነትም ለኢትዮጵያ ጽንስና ማህጸን ሐኪሞች ማህበር የተሰጠበት ሁኔታ ታይቶአል። የአፍሪካው የጽንስና ማህጸን ሕክምና ማህበር ፌደሬሽን በሚቋቋምበት ጊዜ የኢትዮጵያ ጽንስና ማህጸን ሐኪሞች ማህበር አባላት ተሳትፎ ከማድረግም ባሻገር አሁንም በስራ አስፈጻሚ ቦርድ ውስጥ ሁለት የማህበሩ አባላት በመስራት ላይ ናቸው። በአለም አቀፍ የጽንስና ማህጸን ሕክምና ፌደ ሬሽን ውስጥም ለመጀመሪያ ጊዜ ከሰሐራ በታች ያሉ ሐገራትን በመወከል በስራ አስፈጻሚነት ውስጥ ካሉ 6 ኦፊሰሮች ውስጥ አንዱ የኢትዮጵያ የጽንስና ማህጸን ሐኪሞች ማህበር አባል ስለሆነ ይህም ማህበሩ ከአገር ውስጥ እንቅስቃሴው አልፎ በአፍሪካና በአለም አቀፍ ደረጃም ሙያዊ ኃላፊነቱን እየተወጣ ያለ ድርጅት መሆኑን ዶ/ር ደረጀ አብራርተዋል።
 የኢትዮጵያ የጽንስና ማህጸን ሐኪሞች ማህበር 25ኛውን የብር ኢዮቤልዩ እና አመታዊ ጉባኤውን በሚያከብርበት ጊዜ የአፍሪካው የጽንስና ማህጸን ሕክምና ፌደሬሽንም ስብሰባውን አብሮ ያካሂዳል። የአፍሪካው ፌደሬሽን የመጀመሪያውን ስብሰባ ያደረገው እዚሁ አዲስ አበባ ሲሆን በዚያን ጊዜ በስብሰባው የተሳተፉት ወደ 800 የሚሆኑ እንግዶች ነበሩ። የተሳተፉት ሐገራት ብዛትም ወደ 67 ይደርስ ነበር። ሁለተኛው ስብሰባም በኬንያ የተካሄደ ሲሆን አሁን ደግሞ በኢትዮጵያ ሊካሄድ ታቅዶአል። ዶ/ር ይርጉ ገ/ሕይወት የአፍሪካ ጽንስና ማህጸን ሕክምና ፌደሬሽን የመጀመሪው ፕሬዝዳንት የነበሩ ሲሆን አሁንም በአለም አቀፉ የጽንስና ማህጸን ሕክምና ፌደሬሽን ስራ አስፈጻሚነት የሚሰሩ ናቸው።
 እንደዶ/ር ይርጉ ማብራሪያ በአፍሪካ ውስጥ 54 ሀገራት የሚገኙ ሲሆን በአፍሪካው የጽንስና ማህጸን ሕክምና ፌደሬሽን የተወከሉት ግን 32 ሐገራት ብቻ ናቸው። ይህ የሆነበት ምክንያትም ፌደሬሽኑ አባል የሚያደርገው ግለሰቦችን ሳይሆን በማህበር ደረጃ እውቅና ያላቸውን ሐገራት ብቻ ስለሆነ ነው። አንዳንድ ሐገራት ውስጥ በቂ የጽንስና ማህጸን ሐኪም ባለመኖሩ ወይንም በአንዳንድ ሐገራት ደግሞ ቁጥራቸው አነስተኛ በመሆኑ የተነሳ ማህበር ስላልመሰረቱ በአፍሪካ ፌደሬሽን ላይ መወከል አልቻሉም። ስለዚህም በቀጣዮቹ አመታት በየሀገራቱ በሚኖ ረው የጥንካሬ ደረጃ፣ በሚያፈሩት የሰው ኃይል እና በሚመሰርቱት ማህበር መሰረት የሚወ ከሉት ሐገሮች ቁጥር ይጨምራል የሚል ተስፋ አለን። ኢትዮጵያ ግን ፌደሬሽኑ ከመቋቋሙ በፊትም መስፈርቱን ያሟላች ስለነበረች በፌደሬሽኑ ተሳታፊ ሆናለች። ዶ/ር ርጉ ገ/ሕይወት ይህ ጉባኤ በሚካሄድበት ወቅት ስለሚደረጉት አበይት ክንውኖችም እንደሚከተለው ገልጸዋል።
 በኢትዮጵያ የጽንስና ማህጸን ሐኪሞች ማህር 25ኛ አመት በአልና አመታዊ ጉባኤ እንዲሁም በአፍሪካው የጽንስና ማህጸን ሐኪሞች ፌደሬሽን ስብሰባ ላይ ብዙ ሳይንሳዊ ጽሁፎች የሚቀርቡ ሲሆን ህብረተሰቡን እስከአሁን ከነበረው በተሻለ መንገድ ማገልገል እንዲያስችሉ የተነደፉ የተለያዩ ስልጠናዎች ይሰጣሉ።
ብሰባው ከመጀመሩ ሁለት ቀናት በፊት የኢትዮጵያ የጽንስና ማህጸን ሐኪሞች ማህበር አባሎችን በምርምር ስራ ማለትም የምርምር ጽሁፎችን በብቃት እና በጥራት የመጻፍ ክህሎት የሚያገኙበትን ስልጠና በአሜሪካ የጽንስና ማህጸን ኮሌጅ ማህበር ከሚመጡ ባለ ሙያዎች ጋር በመሆን እንሰጣለን። ይህም ምርምራቸውንም በጥራት በአገር ውስ ጥም ይሁን ከአገር ውጭ ለህትመት እንዲያበቁ የሚያስችል እውቀትን የሚያዳብር ነው።
የማህበሩ የስብሰባ መክፈቻ ቀንና ከዚያ አንድ ቀን በፊት በተከታታይ በአልትራሳውንድና የእርግዝና ክትትልን በሚመለከት የላቀ ሕክምና መስጠትን የሚያስችል ስልጠና ማህበሩ ከቅዱስ ጳውሎስ ሚሊኒየም ሜዲካል ኮሌጅ ጋር በመሆን ይሰጣል።
ከሌሎች ሐገሮች ከሚመጡ ተመሳሳይ ሙያ ካላቸው ባለሙያዎች ጋር በመተባበር ማህበሩ የአንድ ቀን ስልጠና ያካሂዳል። በዚሁ ቀን በጥቁር አንበሳ ሆስፒታል ሃቨቋስቈቄ -ቋሰቄቅቨ የሚባለውን የህክምና ዘዴ በሚመለከት በተለይም የማህጸን ችግሮችን ማወቅና መለየት የሚቻልበትን አዲስ ክህሎት ለማህበሩ አባላት የሚሰጥበት ይሆናል።
የጽንስና ማህጸን ድንገተኛ ሕክምናን በተመለከተ ዘመናዊ ወይንም ወቅታዊ የሆኑ እውቀቶች እና ክህሎቶችን በመፈተሽ አሁን ከሚሰራበት በተሻለ ምን ምስራት ይቻላል የሚለውን ማህበሩ ከአሜሪካው የጽንስና ማህጸን ሕክምና ማህበር ጋር በመተባበር ያካሂዳል።
በማህጸን ጫፍ ካንሰርና ከማህጸን ግድግዳ በሚነሳ ካንሰር ላይ ያሉትን ለውጦች ወይንም ወቅታዊ ግኝቶች ከጀርመንና ከአሜሪካ ከሚመጡ ሙያተኞች ጋር በመተባበር ስልጠና ይሰጣል።
በቤተሰብ እቅድ አገልግሎት ላይ በተለይም በቋሚነትና ለረጅም ጊዜ በሚያገለግሉ የቤተሰብ እቅድ ዘዴዎች ላይ ግማሽ ቀን የሚወስድ ስልጠና ይሰጣል።
 ዶ/ር ይርጉ በስተመጨረሻም ለስብሰባው በተያዙት ቀናት እ.ኤ.አ ፌብረዋሪ 2-4 ወይንም ከጥር 25-27 ድረስ ስልጠናውን የሚያገኙት የማህበሩ አባላትና ከሌሎችም ሐገራት የሚመጡ ተሳታፊዎች በጣም ዘመናዊና የመጨረሻ የሆነውን እውቀትና ክህሎት የሚያገኙበት መድረክ ነው። በዚህም ወቅት ወደ 60 የሚደርሱ ጥናታዊ ጽሁፎች በተለያዩ ርእሰ ጉዳዮች ላይ የሚቀርቡ ሲሆን የባለሙያዎችን እውቀት የሚያሰፋ እና ለህብረተሰቡም ጠቃሚ የህክምና አገልግሎትን ለመስጠት የሚያስችል ነው ብለዋል።

Read 2862 times