Monday, 09 January 2017 00:00

ንግድ ባንክ ለልብ ህሙማን ማዕከል የ2.6ሚሊዮን ብር ድጋፍ አደረገ

Written by 
Rate this item
(2 votes)

  የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ዛሬ የሚከበረውን የገና በዓል ምክንያት በማድረግ ጥቁር አንበሳ ሆስፒታል ቅጥር ግቢ ውስጥ ለሚገነባው የልብ ህሙማን ማዕከል የ2.6 ሚ. ብር ድጋፍ ማድረጉን ገለፀ፡፡ ባንኩ በገና ዕለት የሚተላለፍ የበዓል የቴሌቪዥንና የሬዲዮ ፕሮግራም ያዘጋጀ ሲሆን የበዓሉ ቅድመ ቀረፃም ባለፈው ማክሰኞ ረፋድ ላይ በልብ ህሙማን ማዕከል አዳራሽ መከናወኑን የቀረፃውም ምክንያት የገንዘቡ ልገሳ እንደሆነ ባንኩ በላከው መግለጫ አስታውቋል፡፡
ባንኩ በልብ ህመም የሚሰቃዩ ጨቅላ ህፃናትን ለመታደግ ከማዕከሉ ጋር አብሮ እየሰራ መሆኑን ከዚህ ቀደም ድጋፍ ማድረጉን ያስታወሱት የባንኩ ተቀዳሚ ስራ አስኪያጅና ኮሚዩኒኬሽን ሃላፊ አቶ በልሁ ታከለ ይህኛው ድጋፍ የገና በዓልን ምክንያት በማድረግ የተደረገ የልገሳ ልዩ ስነ ስርዓት እንደሆነም ጨምረው ገልፀዋል፡፡
ባንኩ በቀጣይም ለማዕከሉ ድጋፍ ማድረጉን እንደሚቀጥል ለማወቅ ተችሏል፡፡

Read 1256 times