Saturday, 31 December 2016 11:11

ተማሪ ህፃናትን የሚመግበው ድርጅት፣ የአቅም ግንባታ ላይ ሊያተኩር ነው

Written by 
Rate this item
(5 votes)

“ልጆች ባሉበት ሁሉ ምግብ ይኑር” በሚል መሪ ቃል፤ ዘላቂ የት/ቤት ምገባ ፕሮግራም ሲያካሂድ የቆየው የኢትዮጵያ ስኩል ሚል ኢንሼቲቭ (ኢ.ስ.ሚ.ኢ)፤ ተግባሩን ወደ አቅም ግንባታ ስራ ለማሸጋገር እየተንቀሳቀሰ መሆኑን ገልፆ፣ ማዕከሉን ሰቆጣ ለማድረግ ከዋግህምራ ዞን መስተዳደር ጋር በመጪው ማክሰኞ ስምምነት እንደሚፈራረም አስታውቋል፡፡
ህፃናት ተማሪዎችን በየትምሀርት ቤታቸው ሲመግብ የቆየው ማዕከሉ፤ ት/ሚኒስቴር በመጀመሪያ ደረጃ ት/ቤቶች ተመሳሳይ የምገባ ፕሮግራም መጀመሩን ተከትሎ ቀደም ሲል ድርጅቱ ለምገባ ሲጠቀምባቸው የነበሩ ማዕከላቱን ለሰርቶ ማሳያነት እንዲያገለግሉ በማድረግ፣ ፊቱን ወደ አቅም ግንባታ ማዞሩን ገልጿል፡፡
በዋግምሀራ  ዞን በተከሰተው ድርቅ ሳቢያ አካባቢው ይበልጥ ድጋፍ የሚያስፈልገው  ቢሆንም ረሀብን ማሸነፍ እንደሚቻል የተረጋገጠበት አካባቢ በመሆኑ፣ ዞኑ ለመጪዎቹ 3 ዓመታት የኢ.ስ.ሚ.ኢ የስራ ማዕከል ሆኖ የሚዘልቅበትን ስምምነት እንደሚፈረም ታውቋል፡፡


Read 2339 times