Sunday, 25 December 2016 00:00

የዘላለም ጥግ

Written by 
Rate this item
(3 votes)

(ዝነኞች በመሞቻቸው ሰዓት የተናገሩት)

· ‹‹የመጨረሻ ቃል የሚያስፈልገው በህይወት ሳሉ በቅጡ ሳይናገሩ ለቀሩ ጅሎች ነው፡፡››
      ካርል ማርክስ (ፈላስፋ)  
· ‹‹ከሸክላ የተገነባች ሮም አገኘሁ፤ እምነበረዷን ሮምን ትቼላችሁ እሄዳለሁ፡፡››
      አጉስተስ ቄሳር
   (የመጀመሪያው የሮማ ንጉስ፣ ለህዝቡ የተናገረው)
· ‹‹ለመሞት ቅንጣት ታህል አልፈራሁም።››
      ቦብ ማርሊ (ሙዚቀኛ)  
· ‹‹እግዚአብሔርንና የሰው ልጅን አስቀይሜአለሁ፤ ምክንያቱም ሥራዬ ሊኖረው የሚገባው የጥራት ደረጃ ላይ አልደረሰም››  
     ሊዮናርዶ ዳ ቪንቺ  (ፈልሳፊና ሰዓሊ)
· ‹‹ዛሬ ማታ እሄዳለሁ››
     ጄምስ ብራውን (ሙዚቀኛ)
· ‹‹ሁሉም ደስተኛ ነው? ሁሉም ሰው ደስተኛ እንዲሆን እሻለሁ፡፡ እኔ ደስተኛ መሆኔን አውቃለሁ››
    ኢቴል ባሪሞር (ተዋናይት)
· ‹‹አሁን ልተኛ ነው፤ ደህና እደሩ››
    ሎርድ ጆርጅ ባይሮን (ፀሐፊ)
· ‹‹መግባት አለብኝ፤ ጉሙ እየገለጠ ነው››
    ኢሚሊ ዲክንሰን (ገጣሚ)  
· ‹‹እዚያ በጣም ውብ ነው››
   ቶማስ አልቫ ኤዲሰን (ፈልሳፊ)  
· ‹‹አዎ ከባድ ነው፤ ኮሜዲ የመስራት ያህል ግን አይከብድም››   (መሞት ከባድ እንደሆነ ተጠይቆ የመለሰው)
    ኢድመንድ ግዌን (ተዋናይ)
· ‹‹ጥቁር ብርሃን ይታየኛል››
    ቪክቶር ሁጎ (ፀሐፊ)  
· ‹‹ንግስት ነኝ፤ ነገር ግን ክንዶቼን የማንቀሳቀስ ሃይል የለኝም››
    ሉይስ (የፐርሽያ ንግስት)
· ‹‹ምስኪን ነፍሴን ጌታ ይርዳት››
    ኤደጋር አላን ፓ (ፀሐፊ)
· ‹‹ምንም ያልተበረዘ 18 መለኪያ ውስኪ ገልብጫለሁ፤  ይሄ አዲስ ክብረ ወሰን ይመስለኛል….››
    ዳይላን ቶማስ (ገጣሚ)

Read 3433 times