“ለከያንያን እንኳን የመኖሪያ የመቃብር ሥፍራ ማግኘት አስቸጋሪ እንደሆነ በአስናቀች ወርቁ አየሁ” ያሉት የማህበሩ ፕሬዚዳንት ገጣሚና ፀሃፊ ተውኔት አያልነህ ሙላቱ፤ “አርቲስቱ ለምን የራሱ መቀበርያ አይኖረውም” ሲሉ ጠይቀዋል - በዕለቱ ባደረጉት ንግግር፡፡ አንጋፋው የማስታወቂያ ባለሙያ አቶ ውብሸት ወርቃለማሁ ደግሞ፤ የገንዘብ አቅም ያላቸው ወገኖች የበጎ አድራጎት ድርጅቱን እንዲደግፉ እጥራለሁ ካሉ ነኋላ ተለማኙ ለማኝ መሆኑ ያሳዝናል፡፡” ሲሉ ቅሬታቸውን ገልፀዋል፡፡
ልዑል አስፋወሠን አስራተ ካሳ በበኩላቸው፤ “የቀኝ ጌታ ዮፍታሄ ንጉሤ መቃብር ወድቆ ሳይ ነው የዚህ ማህበር አባል ለመሆን ቃል የገባሁት” ብለዋል፡፡
በኢትዮጵያ በተለያየ የኪነጥበብ ዘርፍ የተሰማሩ 10ሺህ ባለሙያዎች እንደሚገኙ ከማህበሩ የተገኘው መረጃ ይጠቁማል፤የኪነጥበባት በጎ አድራጎት ማህበሩ በተቋቋመበት ወቅት የኤፌዲሪ ፕሬዚዳንት ግርማ ወልደጊዮርጊስን የበላይ ጠባቂው ማድረጉ ይታወሳል፡፡