አልዩ ፊልም ፕሮዳክሽን አዘጋጅቶት አቢጌል ኢንተርቴይመንት ያቀረበው “ሰርግ ከአሜሪካ” ፊልም ነገ በአዲስ አበባ የግል ሲኒማ ቤቶችና በመንግስታዊው ስቴሪዮ ሲኒማ እንዲሁም በክልል ከተሞች በተመሳሳይ ሰዓት እንደሚመረቅ አዘጋጆቹ አስታወቁ፡፡ አርቲስት ሳምሶን ታደሰ፣ ኮሜድያን ደረጀ ኃይሌ፣ ቴዎድሮስ ለገሠ ብዙ፣ ፍቃዱ ከበደ፣ ደምሴ በየነና ሌሎች የተወኑበትን የ105 ደቂቃ ፊልም ቴዎድሮስ ለገሠ ብዙ ፅፎት ተሻለ ወርቁ አዘጋጅቶታል፡፡
ፊልሙን ሰርቶ ለማጠናቀቅ አንድ ዓመት ፈጅቷል፡፡