“የሰመጉን ሪፖርት አንቀበልም አላልንም”
ባለፈው ጥቅምት 5 ቀን 2009 ዓ.ም ታትሞ በወጣው አዲስ አድማስ ጋዜጣ ላይ ከሰብአዊ መብቶች ጉባኤ (ሰመጉ) ዋና ዳይሬክተር አቶ ብፅአተ ተረፈ ጋር በተደረገው ቃለ ምልልስ፤ ‹‹ከፕሬዚዳንቱ ፅ/ቤት ሁለተኛ ሪፖርታችሁን ወደ ፅ/ቤታችን እንዳትልኩ ተብለናል›› ሲሉ የተናገሩት የፕሬዚዳንቱን ፅ/ቤት ስም የሚያጠፋና ፈፅሞ ያልተባለ ነገር ነው፤ አንድም ቀን ሪፖርታችሁን አንቀበልም ብለናቸው አናውቅም፤ ልንልም የምንችልበት ምክንያት የለንም፡፡ የፕሬዚንዳንቱ ፅ/ቤት ሁሉንም የሃገሪቱን ዜጎችና ተቋማት በእኩልነት የሚያገለግል ተቋም ነው፡፡
አቶ አለምነህ ረጋሳ የፕሬዚዳንቱ የፅ/ቤት የፕሮቶኮልና ኮሚኒኬሽን ተጠባባቂ ዳይሬክተር፡፡
Published in
ዜና