Monday, 26 September 2016 00:00

‹‹ማልታ ጊነስ›› የ‹‹ስኬት ቦርድ›› ውድድር አካሄደ

Written by 
Rate this item
(0 votes)

    ማልታ ጊነስ በአይነቱ ልዩ የሆነ የስኬት ቦርድ ውድድር ሰሞኑን በአዲስ ስኬት መዝናኛ ውስጥ አካሄደ፡፡ በ15 ተወዳዳሪዎች መካከል የተካሄደው የስኬት ቦርድ ውድድር፤ በአገራችን አምብዛም ያልተለመደውን የስኬት ስፖርት በስፋት እንዲለመድና ብቃት ያላቸው ተወዳዳሪዎችን ለማፍራት የበኩሉን እገዛ እንደሚያደርግ ተገልጿል።
ከአልኮል ነፃ በሆነው የማልታ ጊነስ ምርት ታጅቦ በተካሄደው በዚህ ውድድር ላይ ከ1-3 የወጡ ተወዳዳሪዎች የማልታ ጊነስ ምርት አምራች በሆነው ዲያጆ ኢትዮጵያ የተዘጋጀላቸውን ሽልማቶች ተቀብለዋል፡፡ ውድድሩ በራሳቸው የሚታማመኑና ብቃት ያላቸው የስኬት ቦርድ ስፖርተኞችን ለማፍራት እንደሚያስችል የማልታ ጊነስ ብራንድ ማናጀር አቶ አቤል አናጋው በውድድሩ ወቅት ተናግረዋል፡፡ በዚሁ የስኬት ቦርድ ስፖርት ውድድር ወቅትም ዲያጆ ኢትዮጵያ ለአዲስ ስኬት ፓርክ የ50ሺህ ብር ድጋፍ አድርጓል፡፡

Read 2090 times Last modified on Wednesday, 28 September 2016 07:24