የገጣሚ ትዕግስት ማሞ ሶስተኛ ስራ የሆነው ‹‹የጎደሉ ገፆች›› የግጥም መድበል ከነገ ወዲያ ሰኞ ከቀኑ 11፡30 ጀምሮ በብሔራዊ ቴአትር አዳራሽ ይመረቃል፡፡ በማህበራዊ፣ በፍቅርና በተለያዩ ርዕሰ ጉዳዮች ዙሪያ የሚያጠነጥኑ 23 ያህል ግጥሞችን የያዘው መፅሐፉ፤87 ገጾች ያሉት ሲሆን በ45 ብር ለገበያ ቀርቧል፡፡
በምርቃት ስነ-ስርዓቱ ላይ ደራሲና ሀያሲ አለማየሁ ገላጋይ በመፅሐፉ ላይ ሂሳዊ ዳሰሳ የሚያቀርብ ሲሆን ገጣሚዋን ጨምሮ ኤፍሬም ስዩም፣ ሰለሞን ሳህለ፣ ደምሰው መርሻ፣ ባዩልኝ አያሌው፣ ምስራቅ ተረፈ፣ ምልዕቲ ኪሮስና ሌሎችም የግጥም ስራዎቻቸውን ያቀርባሉ ተብሏል፡፡
Sunday, 18 September 2016 00:00
Published in
ኪነ-ጥበባዊ ዜና