Saturday, 10 September 2016 14:01

“በግል ህይወቴ የማማርረው ዓመት አይደለም”

Written by 
Rate this item
(25 votes)

 ዶ/ር መሸሻ ሸዋረጋ
(የCCRDA ዋና ዳይሬክተር)
ዓመቱ በግል ህይወቴ የተለየ ነገር ባላይበትም፣ የማማርረው አይደለም፡፡ የምመራው CCRDA የልማት ድርጅቶችን የሚያስተባብር እንደመሆኑ፣ በእቅድ ከያዛቸው አብዛኞቹን አሳክቷል፡፡ ያው እንደሚታወቀው፣ እኛ የበጀት ዓመቱን የምንቆጥረው፣በፈረንጆቹ የዘመን ቀመር ነው፡፡ እስካሁን ባለው የስራ ግምገማ፣ ድርጅቱ ካቀደው 80 በመቶውን አሳክቷል፡፡
በግል ህይወቴ፤ ልጄ የ10ኛ ክፍል ብሄራዊ ፈተና ወስዳ፣ በጥሩ ውጤት ወደ መሰናዶ ልትገባ ነው፡፡ ባለቤቴም በእቅዷ መሰረት ሁለተኛ ዲግሪዋን እየሰራች ነው፤ጥሩ ነው፡፡
 በ2009 የማቅደው ፤ስራዬ ህዝብን ከማገልገል ጋር የተያያዘ ስለሆነ፣ እስከ ዛሬ ከምሰራው በተሻለ ሁኔታ በመስራት የተሻለ ውጤት ማስመዝገብ ነው፡፡ ምኞቴ ደግሞ አገራችን ላይ በተለያዩ አቅጣጫዎች የተነሱት ግጭቶችና አለመግባባቶች ተፈትተው፣ አገራችን ላይ ሰላም  ሰፍኖ ማየት ነው፤ ምክንያቱም ያለ ሰላም ልማት የለም፣ እንደ ልብ ወጥቶ መግባት የለም፡፡ አሁን በአገራችን ያለው ሁኔታ እንደ ማንኛውም ኢትዮጵያዊ ያሰጋኛል፤ ያሳስበኛል፡፡ በአዲስ ዓመት ይሄ ሁሉ ችግር ተቀርፎ፤ ሰው ያለ ስጋት ወጥቶ የሚገባበት አገር እንድትሆን እመኛለሁ፡፡ ለመላው የኢትዮጵያ ህዝብ፤ መልካም አዲስ ዓመት እንዲሆንለት እመኛለሁ፡፡

Read 4795 times