Sunday, 04 September 2016 00:00

አቤል ተስፋዬ 2 የዓለም የክብረ-ወሰኖችን አስመዘገበ

Written by 
Rate this item
(2 votes)

   በርካታ ታላላቅ ዓለማቀፍ የሙዚቃ ሽልማቶችን በማስገባት ስኬታማ የሙዚቃ ጉዞውን የቀጠለው ትውልደ ኢትዮጵያዊው ድምጻዊ አቤል ተስፋዬ፤ በ2017 የዓለም የክብረወሰን መዝገብ በሁለት ክብረ ወሰኖች መመዘግቡን ተቋሙ ባወጣው መግለጫ አስታውቋል፡፡
ዘ ዊክንድ በሚል ቅጽል ስሙ የሚታወቀው የ26 አመቱ ድምጻዊ፤ “ቢዩቲ ቢሃይንድ ዘ ማድነስ” በሚለው የሙዚቃ አልበሙ ባለፈው የፈረንጆች አመት በ“ስፖቲፋይ” ድረገጽ ተጠቃሚዎች በብዛት በመታየቱና ሙዚቃዎቹ በቢልቦርድ የሙዚቃ ሰንጠረዥ ለረጅም ተከታታይ ሳምንታት በምርጥ አስር ዝርዝር ውስጥ በመቆየታቸው፣ በአለም የክብረ ወሰን መዝገብ ላይ በሁለት ክብረ ወሰኖች ስሙን ማስፈሩ ተገልጧል፡፡
“ቢዩቲ ቢሃይንድ ዘ ማድነስ” የተሰኘው የአቤል የሙዚቃ አልበም ከታህሳስ 2014 እስከ ታህሳስ 2015 ባለው አንድ አመት ጊዜ ውስጥ በ60 ሚሊዮን የ“ስፖቲፋይ” ተጠቃሚዎች በመታየት ክብረ ወሰን ማስመዝገቡን የጠቆመው ተቋሙ፣ የድምጻዊው ዘፈኖች ከመጋቢት 2015 እስከ ጥር 2016 ባሉት ጊዚያት፣ ለ45 ተከታታይ ሳምንታት በቢልቦርድ የሙዚቃ ሰንጠረዥ ምርጥ አስር ደረጃ ውስጥ ተካትተው መቆየታቸውን ገልጧል፡፡

Read 2297 times