Sunday, 21 August 2016 00:00

23 ደቡብ ሱዳናውያን 10 ኢትዮጵያውያንን በመግደል ተከሰሱ

Written by 
Rate this item
(8 votes)

ግድያውን የፈጸሙት ለበቀል ነው ተብሏል

ባለፈው ሚያዝያ ወር ላይ በጋምቤላ ክልል በሚገኝ የስደተኞች የመጠለያ ጣቢያ የሚሰሩ 10 ኢትዮጵያውያንን በአሰቃቂ ሁኔታ ገድለዋል የተባሉ 23 ደቡብ ሱዳናውያን ስደተኞች ባለፈው ሰኞ በግድያ ወንጀል መከሰሳቸውን ሮይተርስ ዘገበ፡፡
በጋምቤላ ጀዊ የስደተኞች የመጠለያ ጣቢያ ውስጥ ሁለት ደቡብ ሱዳናውያን ህጻናት በመኪና አደጋ ለህልፈተ ህይወት መዳረጋቸውን ያስታወሰው ዘገባው፣ እነዚሁ 23 ደቡብ ሱዳናውያንም የህጻናቱን ሞት ለመበቀል በማሰብ፣ በስደተኞች ጣቢያው ውስጥ ተቀጥረው የሚሰሩ 10 የግንባታ ሰራተኞችን በአሰቃቂ ሁኔታ ደብድበው በመግደላቸው ክስ እንደተመሰረተባቸው ጠቁሟል፡፡
በተከሳሾቹ የግድያ ሰለባ የሆኑት አስሩ ኢትዮጵያውያን በህጻናቱ ግድያ ላይ እጃቸው እንደሌለበት የክስ መዝገቡ መግለጹን የጠቆመው ዘገባው፤ ግድያው መፈጸሙን ተከትሎ በአካባቢው ብጥብጥ መፈጠሩንና አንዳንድ ደቡብ ሱዳናውያን ስደተኞችም ጥቃት እንደደረሰባቸው አስታውሷል፡፡ በደቡብ ሱዳንያውያኑ ስደተኞች ከተገደሉት 10 ንጹሃን ኢትዮጵያውያን መካከል ሁለቱ ሴቶች መሆናቸውም ተነግሯል፡፡ በጋምቤላ ክልል ከ270 ሺህ በላይ ደቡብ ሱዳናውያን ስደተኞች እንደሚገኙም ዘገባው አስታውሷል፡፡


Read 3889 times