Monday, 22 August 2016 00:00

“የዓመቱ በጎ ሰው ሽልማት” አሸናፊዎች ነሐሴ 28 ይታወቃሉ

Written by 
Rate this item
(7 votes)

ለአራተኛ ጊዜ የሚካሄደውና ለሀገራቸውና ለወገናቸው ላቅ ያለ አገልግሎት የሰጡ ዜጎች የሚከበሩበት የዓመቱ በጎ ሰው ሽልማት ሥነሥርዓት ነሐሴ 28 ቀን 2008 ዓ.ም በአዲስ አበባ አቤል ሲኒማ ይከናወናል፡፡
በ10 ዘርፎች ለ2008 የዓመቱ በጎ ሰው ሽልማት መብቃት አለባቸው የተባሉ ዜጎች በሕዝቡ የተጠቀሙ ሲሆን በየዘርፉ ከተጠቆሙት ዜጎች መካከልም ሥራዎቻቸው ተመዝነው በሽልማት ኮሚቴው አማካኝነት ሦስት ሦስት ዕጩዎች ተለይተዋል፡፡
በእነዚህ እጩዎች ላይ አምስት አምስት ዳኞች (በየዘርፉ) ድምጽ እየሰጡ መሆኑ የታወቀ ሲሆን የየዘርፉ ተሸላሚዎችም ነሐሴ 28 ቀን 2008 ዓ.ም በሚኖረው ሥነ ሥርዓት ይታወቃሉ ተብሏል። ሚዲያዎችና ሌሎች የመገናኛ አካላት፣እጩዎችን በማስተዋወቅና በማክበር፣ ለሀገራቸው በጎ የሚሠሩ ዜጎችን ለማብዛት የበኩላቸውን እንዲወጡ የበጎ ሰው ሽልማት ኮሚቴ ጠይቋል፡፡ ከዚህ በታች እጩዎቹ በየዘርፋቸው ቀርበዋል፡፡
መምህርነት
ተ/ ፕሮፌሰር ዘሪሁን አስፋው
ተ/ ፕሮፌሰር መረራ ጉዲና
መ/ር አውራሪስ ተገኝ
ንግድና ሥራ ፈጠራ
አቶ ብዙአየሁ ታደለ
አቶ ሳሙኤል ታፈሰ
አቶ ኢየሱስ ወርቅ ዛፉ
ማኅበራዊ ጥናት
ፕሮፌሰር ጌታቸው ኃይሌ
ዶክተር አንዳርጋቸው ጥሩነህ
ፕሮፌሰር ባየ ይማም
ሳይንስ
ሎሬት ዶክተር መላኩ ወረደ
ዶክተር ዓለማየሁ ዋሴ
ዶክተር ውዱ ዓለማየሁ
ቅርስና ባሕል
የኢትዮጵያ ጥናት ተቋም (አዲስ አበባ     
           ዩኒቨርሲቲ)
ኢንጅነር ታደለ ብጡል
መ/ር ካሕሳይ ገብረ እግዚአብሔር
መንግሥታዊ የሥራ ኃላፊነትን በብቃት መወጣት
ኢንጅነር ዘውዴ ተክሉ
ዶክተር ተወልደ ብርሃን
          ገብረእግዚአብሔር
ዳኛ ስንታየሁ ዘለቀ
ስፖርት
አቶ ጌቱ በቀለ
ጋቶች ፓኖ
ዶክተር ይልማ በርታ
ኪነጥበብ (ድርሰት)
አቶ አስፋው ዳምጤ
ወ/ሮ ፀሐይ መላኩ
አቶ አውግቸው ተረፈ
ሚዲያና ጋዜጠኛነት
መንሱር አብዱልቀኒ
አቶ አጥናፍሰገድ ይልማ
አቶ ደረጀ ኃይሌ
በጎ አድራጎት
ዶክተር ቦጋለች ገብሬ
ወ/ሮ ፀሐይ ሮቺሊ
ወ/ሮ ዘውዲቱ መሸሻ

Read 2605 times