Monday, 22 August 2016 00:00

8 ግብጻውያን ሴት ጋዜጠኞች በውፍረታቸው ሰበብ ከስራ ታገዱ

Written by 
Rate this item
(8 votes)

 - ያለቅጥ ወፍራችኋል፤ ሸንቀጥ እስክትሉ ህዝብ ፊት አትቀርቡም ተብለዋል
   የግብጽ መንግስት የብሮድካስቲንግ ተቋም የሆነው “ኢርቱ”፤8 ሴት የአገሪቱ የቴሌቪዥን ጣቢያ ጋዜጠኞችን “ያለቅጥ ወፍራችኋል፣ የምትመገቡትን ምግብ መጠን ቀንሳችሁ እስክትከሱና ሸንቀጥ እስክትሉ ድረስ ከህዝብ ፊት አትቀርቡም” በሚል ለአንድ ወር ያህል ጊዜ ከስራ ማገዱን ቢቢሲ ዘገበ፡፡
“ዘ ኢጂፕሺያን ሬዲዮ ኤንድ ቴሌቪዥን ዩኒየን” የተባለው ተቋም ይሄን አስቀያሚ ውፍረታችሁን ይዛችሁ ከተመልካች ፊት አትቀርቡም በሚል በጋዜጠኞቹ ላይ የወሰደው ከስራ የማገድ እርምጃ፣የሴቶች መብቶች ተከራካሪ ቡድኖችን ማስቆጣቱን ዘገባው ጠቁሟል፡፡
“ዘ ውሜንስ ሴንተር ፎር ጋይዳንስ ኤንድ ሌጋል አዌርነስ” የተባለው የአገሪቱ የሴቶች መብት ተከራካሪ ቡድን፣ ውሳኔው ህገ-መንግስትን የሚጥስና በግብጻውያን ሴቶች ላይ የተቃጣ ጾታዊ ጥቃት ነው ሲል ተቃውሞውን በማሰማት ውሳኔው እንዲሻር ጥያቄ ማቅረቡን ዘገባው አመልክቷል፡፡ ጥያቄው የቀረበለት ተቋም ግን ውሳኔው በምንም አይነት መንገድ እንደማይሻር ማስታወቁን ቬቶ ኒውስ የተባለው የግብጽ ድረገጽ የዘገበ ሲሆን፣ የአገሪቱ የመገናኛ ብዙሃን ተቋማትና ጋዜጠኞች በጉዳዩ ዙሪያ እየተከራከሩ እንደሚገኙም ተነግሯል፡፡

Read 3613 times