Monday, 08 August 2016 05:32

ዲማ ልዩ የዓይን ህክምና ማዕከል ስራ ጀመረ

Written by 
Rate this item
(3 votes)

    በአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ የአይን ህክምና መምህሮች የተቋቋመው “ዲማ” የአይን ህክምና ክሊኒክ፤ሙሉ በሙሉ ስራ መጀመሩን አስታወቀ፡፡ ክሊኒኩ ከሌላው የአይን ህክምና በተለየ በአይን ቆብና በእንባ መፍሰስ ህክምና ላይ ትኩረት አድርጎ እንደሚሰራና በአገሪቱ ሁለቱ ህክምናዎች ላይ ስፔሻላይዝድ ያደረጉ ሁለት ኢትዮጵያዊያን ዶክተሮች ብቻ እንዳሉ የክሊኒኩ መስራች አባል ዶ/ር መሰረት እጅጉ ሰሞኑን ለጋዜጠኞች በሰጡት መግለጫ አስታውቀዋል፡፡ በአሁኑ ወቀት የእንባ መፍሰስ፣ የአይን ቆብና የአይን ቆብ አካባቢዎችን በማከም ትኩረት ያደረገው ክሊኒኩ፣ ሌሎችንም የአይን ህክምናዎች እግረ መንገዱን እንደሚሰጥና በተለያዩ አደጋዎች አይናቸውን ያጡ ሰዎች፣ በቀዶ ጥገና አርቴፊሻል አይኖችን እንደሚተክሉ ዶ/ር መሰረት ተናግረዋል፡፡

Read 1960 times