Saturday, 30 July 2016 13:54

ሃሳብዎን በ‹‹ነፃነት›› ይግለፁ!

Written by 
Rate this item
(16 votes)

(በ‹‹ፖለቲካ በፈገግታ›› ስታይል የተዘጋጀ
አስተያየት መሰብሰቢያ)

1. የአዲስ አበባ አስተዳደር ‹‹ህገ ወጥ›› ቤቶች
በሚላቸው ላይ እየወሰደ ያለውን በጅምላ
የማፍረስ እርምጃ በተመለከተ አስተያየትዎ
ምንድን ነው?
ሀ ) ለ ድሆች እ ቆረቆራለሁ የ ሚል
መንግስት፤ዜጎችን በሃምሌ ጨለማ
ያፈናቅላል ብዬ አልጠበቅሁም!
ለ) ማፍረሱ ሳያንስ ነዋሪዎቹ ሁለት ሶስት ቤት
ያላቸው፤‹‹ቱጃሮች›› ናቸው ማለቱ
አስገርሞኛል!
ሐ) እርምጃው ተገቢ ነው! ህገ ወጦች ዝም
ከተባሉ ማዘጋጃ ቤት አጠገብ ህገ ወጥ
ቤት ከመገንባት አይመለሱም
መ) “ህገወጥ ቤቶች” ሲስፋፉ ዝም ያሉ
የወረዳ ሃላፊዎች፣ቤቶቹ ሲፈርሱ
ከሃላፊነታቸው መነሳት ነበረባቸው!
ሠ) ብዙ ሺህ ስደተኞች ተቀብላ የምታስተናግድ
አገር፤እንዴት ለዜጎቿ መሆን
ያቅታታል!?
2. መዲናዋ ከሳምንት በላይ ቆሻሻ የምትጥልበት
አጥታ፣በአጣብቂኝና በስጋት ውስጥ መሰንበቷ
ከምን የመጣ ይመስልዎታል?
ሀ) ከመልካም አስተዳደር ችግር!
ለ) ግልፅነት ከጎደለው አሰራር!
ሐ) ከድርድር ጥበብ ማነስ
መ) ከአመራር ክሽፈት
ሠ) እኔ ምን አውቅላቸዋለሁ!
3. ከሚከተሉት ውስጥ የአውራው ፓርቲ የከፋ
ችግሩ የትኛው ነው ይላሉ?
ሀ) ልማታዊ ጀብደኝነቱ
ለ) እውነታውን በፕሮፓጋንዳ መጨፍለቁ
ሐ) አጉል ፍረጃና ጠላት ማብዛቱ
መ) ለዚህች አገር “ከእኔ በላይ ላሳር” ማለቱ
ሠ) ምን ያልከፋ ችግር አለው!
4. ኢህአዴግ መራሹን መንግስት የማይገልፀው
ባህሪ የትኛው ይመስልዎታል?
ሀ) ለመጪው ትውልድ ምቹ አገር መፍጠር
ለ) ጥልቅ የአገር ፍቅር ስሜት
ሐ) ለዜጎች መቆርቆርና ቅድምያ መስጠት
መ) ከአገር በፊት ፓርቲን ማስቀደም
ሠ) እኔ ባህሪው ገብቶኝ አያውቅም!
(ማስታወሻ፡- ለእርስዎ የሚስማማ መልስ
ከምርጫዎቹ ውስጥ ካላገኙ የራስዎትን መልስ
ማካተት ይችላሉ፡፡)

Read 3560 times