Monday, 25 July 2016 09:11

ማይክሮሶፍት ባለፉት 3 ወራት 3.1 ቢሊዮን ዶላር ትርፍ አግኝቷል

Written by 
Rate this item
(2 votes)

   ታዋቂው የቴክኖሎጂ ኩባንያ ማይክሮሶፍት፣ ባለፉት ሶስት ወራት ብቻ 3.1 ቢሊዮን ዶላር ትርፍ ማግኘቱን የኩባንያው ዋና ስራ አስፈጻሚ ሳትያ ናዴላ ማክሰኞ ዕለት ይፋ ማድረጋቸውን አጃንስ ፍራንስ ፕሬስ ዘገበ፡፡
ኩባንያው በተጠናቀቀው ሩብ አመት 20.6 ቢሊዮን ዶላር አጠቃላይ ገቢ ማግኘቱን ያስታወቁት ናዴላ፤ባለፈው አመት ተመሳሳይ ወቅት ያገኘው ገቢ ግን 22.2 ቢሊዮን ዶላር እንደነበር አስታውሰዋል፡፡
ማይክሮሶፍት ኩባንያ በተጠቀሰው ጊዜ ውስጥ ያገኘዋል ተብሎ ከተገመተው በላይ ገቢ ማግኘቱ የተገለጸ ሲሆን ገቢው ሊያድግ የቻለውም የምርታማነትና በቢዝነስ ፕሮሰስ ክፍሉ ያከናወነው ስራ ውጤታማነት እንደሆነ ተጠቁሟል፡፡ ማይክሮሶፍት ባለፉት ሶስት ወራት ከጌሞች ሽያጭ ያገኘው ገቢ በ9 በመቶ ቢቀንስም፣ ከማስታወቂያ ያገኘው ገቢ በአንጻሩ በ54 በመቶ እድገት ማሳየቱ ተነግሯል፡፡
ኩባንያው ባለፈው ሰኔ ወር በ26 ቢሊዮን ዶላር ሊንክዲን የተባለውን ማህበራዊ ድረገጽ መግዛቱን ያስታወሰው ዘገባው፤ ይህም በቀጣይ ገቢውን ያሳድግለታል ተብሎ እንደሚጠበቅ አስታውቋል፡፡





Read 3344 times