Error
  • JUser: :_load: Unable to load user with ID: 62
Monday, 05 March 2012 13:23

የተወገዘው ሳቻ ባሮን በአምባገነኖች ላይ ፊልም ሰራ

Written by 
Rate this item
(0 votes)

በኦስካር ምሽት እንደጋዳፊ ባለሙሉ ማዕረግ ወታደራዊ ትጥቅ ለብሶ እና በሴት ቦዲ ጋርዶች በመታጀብ በቀዩ ምንጣፍ ላይ የተመላለሰው እንግሊዛዊው ኮሜድያን ሳቻ ባሮን ኮሐን ተወገዘ፡፡ ኮሜድያኑን በኦስካር እንግድነት ሲጋበዝ አላግባብ ይረብሻል በሚል የስነስርዓቱ አዘጋጆች ሊያግዱት አቅማምተው ነበር፡፡ እንደ ጋዳፊ ከመልበሱ ባሻገር በቅርቡ የሞቱትን የሰሜን ኮርያ መሪ ኪምጆንግኢል ፎቶ ያለበትን ማሰሮ መሸከሙ አነጋጋሪ ሆኗል፡፡ ሳቻ ባሮን ይህን ተግባር የፈፀመው ከወር በኋላ ለእይታ የሚበቃ አዲስ ፊልሙን  “ዘ ዲክታተር” ለማስተዋወቅ በማሰቡ ከሆነ ተሳክቶለታል ተብሏል፡፡ ኮሜዲያኑ በተለያዩ የቀልድ ተግባራቱ ፈር ስቷል የሚሉ ሃያሲዎች ለባህል ክብር የሚነፍግ አንዳንዴም ከመስመር የወጣ በማለት ይተቹታል፡፡

“ዘ ዲክታተር› ሳቻ ባሮን በአሜሪካ የሰራው 3ኛው የኮሜዲ ፊልሙ መሆኑን የገለፀው ዘ ሆሊውድ ሪፖርተር በዓለማችን አምባገነን መሪዎች ላይ ሰፊ ትችት እንደሚታይበት ጠቁሟል፡፡ የሳቻ ባሮን በአሜሪካ የተሰራ የመጀመርያ ፊልም በርእሱ ረጅምነት የሚታወቀው‹ ካልቸራል ለርኒንግ ኦፍ አሜሪካ ፎር ሜክ ቤነፊት ግሎርየስ ኔሽን ኦፍ ካዛኪስታን” ሲሆን በ18 ሚሊዮን ዶላር በጀት ተሰርቶ 280 ሚሊዮን ዶላር በመላው ዓለም ገቢ ሆኖበታል፡፡ ከወር በኋላ የሚታየው ዘ ዲክታተር በቀድሞው የኢራቅ መሪ ሳዳም ሁሴን በተፃፈው “ዘቢባህ ኤንድ ዘ ኪንግ” የተባለ መፅሃፍን በመንተራስ ተሰርቷል፡፡ በፊልሙ ላይ በመሪ ተዋናይነት ለሰራው ሳቻ ባሮን 20 ሚሊዮን ዶላር ተከፍሏል ያለው “ዘ ሆሊውድ ሪፖርተር” የኮሜድያኑ ክፍያ የሆሊውድ ትልቅ ተከፋዮቹ ቶም ክሩዝና ጆኒ ዲፕ መቀራረቡ አስገራሚ ነው ብሏል፡፡

 

 

 

Read 1239 times Last modified on Monday, 05 March 2012 13:27