Saturday, 09 July 2016 09:49

ጅማ ዩኒቨርሲቲ በሁለተኛ ዲግሪ፤ 136 ተማሪዎችን ነገ ያስመርቃል

Written by 
Rate this item
(5 votes)

   ጅማ ዩኒቨርሲቲ ከኤቢኤች ሰርቪስ ጋር በመተባበር በሁለት የድህረ ምረቃ ፕሮግራሞች ያስተማራቸውን 136 ተማሪዎች ነገ በሸራተን አዲስ ያስመርቃል፡፡
በማስተርስ ኦፍ ቢዝነስ አድሚኒስትሬሽንና በማስተርስ ኦፍ ፐብሊክ ኸልዝ የሚመረቁት እነዚሁ የድህረ ምርቃ ተማሪዎች፤ ላለፉት ሁለት ዓመታት በአዲስ አበባ ኤቢኤች ካምፓስ ትምህርታቸውን ሲከታተሉ የቆዩ ናቸው፡፡
ዩኒቨርሲቲው የረጅም ዓመታት ሙያዊ እውቀትና ልምድ ያላቸውን መምህራን በመመደብ ተማሪዎቹን በማስተማር ላይ እንደሚገኝ የገለፁት የዩኒቨርሲቲው ፕሬዚዳንት ፕሮፌሰር ፍቅሬ ለሜሳ፤ አሁንም አዳዲስ ፕሮግራሞችን በመክፈት የመንግስትና የግል ዘርፉን አጋርነት ወደ ላቀ ደረጃ ለማድረስ እንደሚሰራ ገልፀዋል፡፡
 የኤቢኤች ሰርቪስ ዋና ሥራ አስፈፃሚ ዶ/ር ማርቆስ ፈለቀ በበኩላቸው፤ የጅማ ዩኒቨርሲቲን ወደ አዲስ አበባ መምጣት ተከትሎ የድህረ ምረቃ ተማሪዎች ፍላጎት ከጊዜ ወደ ጊዜ እየጨመረ መሄዱን ጠቁመው፤ በቀጣዩ በሁለት የድህረ ምርቃ ፕሮግራሞ በፐብሊክ ሪሌሽንና ኮርፖሬት ኮሚዩኒኬሽን እንዲሁም በኸልዝ ሞኒተሪንግና ኢቫሉዬሽን አዳዲስ ተማሪዎን እንደሚቀበል ተናግረዋል፡፡
ዩኒቨርሲቲው በነገው ዕለት ከሚያስመርቃቸው የድህረ ምረቃ ተማሪዎች መካከል 42ቱ ሴቶች ሲሆኑ ባለፈው ዓመት ለመጀመሪያ ጊዜ 97 ተማሪዎችን በሁለተኛ ዲግሪ አስተምሮ ማስመረቁ አይዘነጋም፡፡ 

Read 1764 times