Saturday, 18 June 2016 12:31

“የስንብት ቀለማት” ለንባብ ሊበቃ ነው

Written by 
Rate this item
(9 votes)

- በኢትዮጵያ የስነ-ጽሁፍ ታሪክ ረጅሙ ልብወለድ ነው

   በአንጋፋው ደራሲ አዳም ረታ የተጻፈውና ዘጠነኛ ስራው የሆነው “የስንብት ቀለማት” የተሰኘ የረጅም ልቦለድ መጽሃፍ በቅርቡ ለንባብ እንደሚበቃ ደራሲው ለአዲስ አድማስ  መግለጫ አስታወቀ፡፡
ደራሲ አዳም ረታ ከሁለት አስርት አመታት በላይ ሲያስተዋውቀው የነበረውን ‘ሕጽናዊነት’ የተባለ ልዩ የአጻጸፍ ስልት በስፋትና በጥልቀት ያሳየበት “የስንብት ቀለማት”፣ በቅርጹም ሆነ በይዘቱ የተለየ እንደሚሆን የተነገረ ሲሆን ደራሲው ከዚህ ቀደም ባሳተማቸው መጽሃፍት ውስጥ የሚጠቀማቸው ምስሎች፣ ቻርቶች፣ ግራፊክ ዲዛይኖችና ሰንጠረዦች በአዲሱ መጽሀፍም መካተታቸውንና ባለ ሙሉቀለም የግርጌ ስታወሻዎችና ሌሎች አዳዲስ ይዘቶች እንዳሉት ታውቋል፡፡
በመጨረሻ ገፆቹ የአንጋፋውን የአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ የስነጽሁፍ መምህር ረዳት ፕሮፌሰር ቴዎድሮስ ገብሬ ዳሰሳ “ድሕረ ቃል” በሚል ርዕስ ያካተተው መፅሀፉ ፤ በ960 ገጾች በኢትዮጵያ የሥነ ፅሁፍ ታሪክ ረዥሙ ልብወለድ ለመሆን በቅቷል፡፡  8 አቢይ ምዕራፎችና 46 ንኡስ ምዕራፎች ያሉት ልብ ወለዱ፤ ዋጋው 350 ብር እንደሆነ ታውቋል፡፡

Read 5094 times