Saturday, 28 May 2016 15:04

የአቶ አንዳርጋቸው ጽጌ ልጅ የእንግሊዝን መንግስት ልትከስ ነው

Written by 
Rate this item
(13 votes)

   በየመን በኢትዮጵያ መንግስት በቁጥጥር ስር የዋሉትና በእስር ላይ የሚገኙት የአቶ አንዳርጋቸው ጽጌ ልጅ የሆነቺው የ9 አመቷ ታዳጊ ምናበ አንዳርጋቸው፤ አባቴ ከእስር የሚፈታበትን መንገድ አላመቻቸም በሚል የእንግሊዝን መንግስት ልትከስ እንደሆነ ዘ ኢንዲፔንደንት ዘገበ፡፡ የታዳጊዋ የህግ ባለሙያዎች የእንግሊዝ መንግስት የአቶ አንዳርጋቸውን ጉዳይ የሚገባውን ያህል አለመከታተሉና ከእስር የሚፈቱበትን መንገድ ለመፈለግ እስከመጨረሻው አለመግፋቱ በህግ ያስጠይቀዋል ማለታቸውን የጠቆመው ዘገባው፣ የእንግሊዝን መንግስት በህግ መጠየቁ፣ አቶ አንዳርጋቸው ከእስር የሚፈቱበትን ሁኔታ ለመፍጠር ያስችላል የሚል ተስፋ እንዳላቸው መናገራቸውን ገልጧል፡፡
በእንግሊዝ የውጭና የኮመንዌልዝ ቢሮ ፤የአቶ አንዳርጋቸው እስርና አያያዝ ተቀባይነት የሌለው ነው ቢልም፣ ከእስር ተፈትተው እንዲወጡ ግፊት አላደረገም ያለው ዘገባው፣ ልጃቸው ምናበ፤ አባቷ የሚፈቱበትን ሁኔታ ለመፍጠር ተጨማሪ ጥረት ያደርጋል በሚል ተስፋ መንግስትን ለመክሰስ መዘጋጀቷን ጠቁሟል፡፡

Read 6309 times