ዲቢኤል ግሩፕ የተባለው ታዋቂ የባንግላዴሽ የጨርቃ ጨርቅና አልባሳት አምራች ኩባንያ በትግራይ ክልል ከ2 ቢሊዮን ብር በላይ የሚያወጣ የጨርቃ ጨርቅና አልባሳት ፋብሪካ ሊገነባ መሆኑን ዴይሊ ስታር ድረገጽ ትናንት ዘገበ፡፡
በቀጣዩ አመት የካቲት ወር ላይ ግንባታው ሙሉ ለሙሉ ተጠናቆ የማምረት ስራ ይጀምራል ተብሎ የሚጠበቀው የጨርቃ ጨርቅና የአልባሳት ፋብሪካው፤ ለ3 ሺህ 500 ሰራተኞች የስራ ዕድል እንደሚፈጥር የኩባንያው ከፍተኛ የስራ ሃላፊ መናገራቸውን ዘገባው አመልክቷል፡፡
ኩባንያው ለፋብሪካው ግንባታ ከኢትዮጵያ ልማት ባንክ ካገኘው 55 ሚሊዮን ዶላር ብድር በተጨማሪ የ15 ሚሊዮን ዶላር ብድር ከስዊድን መንግስት የልማት ፈንድ ማግኘቱን የጠቆመው ዴይሊስታር፣ ምርቶቹን ወደተለያዩ የአውሮፓ፣ የአፍሪካ፣ የመካከለኛው ምስራቅ ሃገራትና ወደ አሜሪካ ኤክስፖርት ለማድረግ ማቀዱንም አስታውቋል፡፡
Published in
ዜና