Saturday, 28 May 2016 09:40

ማህሙድ አህመድ ከጎንደር ዩኒቨርሲቲ የክብር ዶክትሬት ተቀበለ

Written by 
Rate this item
(6 votes)

         አንጋፋው ድምጻዊ ማህሙድ አህመድ፤የክብር ዶክትሬቱን ከጎንደር ዩኒቨርሲቲ ትላንት ተቀበለ፡፡ ጎንደር ዩኒቨርሲቲ አርቲስቱ ላበረከተው ድንቅና የረጅም ጊዜ የኪነ ጥበብ ስራ በ2007 ዓ.ም መጨረሻ ላይ ተማሪዎቹን ሲያስመርቅ፣ የክብር ዶክትሬት ከሰጣቸው አራት ሰዎች አንዱ አንደነበር የሚታወስ ሲሆን ማህሙድ በወቅቱ በአገር ውስጥ ባለመኖሩ ተወካዩ በሥነ ስርዓቱ ላይ ተገኝተው እንደነበረ የዩኒቨርሲቲው የህዝብና ዓለም አቀፍ ግንኙነት ዳይሬክቶሬት ዳይሬክተር አቶ ደምሴ ደስታ ለአዲስ አድማስ ተናግረዋል፡፡ በትላንትናው እለት አርቲስቱ ራሱ በአካል ተገኝቶ ከዩኒቨርሲቲው የክብር ዶክትሬቱን ተቀብሏል፡፡ በዚህ ሥነ ስርዓት ላይ የቀድሞው የጎንደር ፋሲለደስ የኪነት ቡድን ዳግም  ምስረታም ተካሂዷል፡፡ ማህሙድ አህመድ፤ በቅርቡ 75ኛ ዓመት የልደት በዓሉን ሲያከብር በማሪዮት ሆቴል ለእይታ ከቀረቡት 75 ፎቶዎቹ መካከል 40 ያህሎ በጎንደር ሥነ ሥርዓቱን ምክንያት በኤግዚቢሽን መልክ ለእይታ የቀረቡ ሲሆን ለአንድ ሳምንት ለተመልካች ክፍት ሆነው እንደሚቆዩም አቶ ደምሴ ጨምረው ገልፀዋል፡፡ በሥነ-ሥርዓቱ ላይ በርካታ አርቲስቶች፣ ታዋቂ ሰዎችና ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች ተገኝተዋል፡፡  

Read 1900 times