Saturday, 21 May 2016 17:26

የካምቦዲያ መሪና ሚስታቸው በሙሉ ማዕረግ እንዲጠሩ ታዘዘ

Written by 
Rate this item
(4 votes)

  ይህን የማያደርጉ መገናኛ ብዙኃን እርምጃ ይወሰድባቸዋል
        በካምቦዲያ የሚገኙ መገናኛ ብዙኃን የአገሪቱን ጠቅላይ ሚኒስትር በተመለከተ በሚሰሯቸው ዘገባዎች ላይ ተገቢውን ክብር መስጠት እንደሚገባቸውና ሙሉ ማዕረጋቸውን መጥቀስ እንዳለባቸው በአገሪቱ የመረጃ ሚኒስቴር ትዕዛዝ እንደተሰጣቸው ቢቢሲ ዘገበ፡፡ሚኒስቴሩ ለአገሪቱ የህትመትና የኤሌክትሮኒክስ መገናኛ ብዙኃን በሰጠው መግለጫ እንዳሳሰበው፣ ከመጪው ነሐሴ ወር ጀምሮ በሚሰሯቸው ዘገባዎች ላይ የጠቅላይ ሚኒስትሩን፣ የባለቤታቸውንና የተወሰኑ ባለስልጣናትን ከእነ ሙሉ ማዕረጋቸው መጥራት ይገባቸዋል፡፡መገናኛ ብዙኃኑ የአገሪቱን መሪ በተመለከተ በሚሰሯቸው ዘገባዎች ላይ፣ “ጌታ ጠቅላይ ሚኒስትርና የጠቅላይ ጦር አዛዥ ሁን ሴን” በማለት ከነ ሙሉ ማዕረጋቸው እንዲጠሯቸው ማሳሰቢያ እንደተሰጣቸው የጠቆመው ዘገባው፣ ሚኒስቴሩ ይህን በማያደርጉ መገናኛ ብዙኃን ላይ እርምጃ እንደሚወሰድ ቢናገርም እርምጃውን በተመለከተ የጠቀሰው ነገር እንደሌላ አመልክቷል፡፡

Read 2711 times