በኢትዮጵያና በጣሊያን ጦርነት ወቅት በኢትዮጵያ ወገን ሆኖ ለ11 ወራት ተጋድሎ ያደረገው
ኩባዊ ኮሎኔል አሌኸንድሮ ዴል ባዬ በስፓኒሽ ቋንቋ በ1929 ዓ.ም “አንድ ነጭ በጥቁሮች የሰቆቃ ምድር”
በሚል ያሳተመውና በተስፋዬ መኮንን ባይለዬኝ “ቀይ አንበሳ” በሚል ወደ አማርኛ የተተረጎመው
መፅሀፍ ለአራተኛ ጊዜ ታትሞ ለንባብ በቃ፡ ፡ የ መጀመሪያው እ ትም በ 1992 ዓ .ም ሁ ለተኛው
በ2003፣ ሶስተኛው በ2004 ታትሞ ተወዳጅነትን አትርፎ የነበረ ሲሆን ሰሞኑን ለአራተኛ ጊዜ ታትሞ
ለንባብ በቅቷል መፅሀፉ ኪባዊው ኮሎኔል በ11 ወራት ውስጥ ባሳለፈው የጦርነት ተጋድሎ በአይኑ ያያቸውን እና የተሳተፈባቸውን አስገራሚ ሁነቶች የተረከበት ሲሆን በፎቶ ማስታዎሻዎች የተደገፈም ነው በ317 ገፅ የተቀነበበው መፅሀፉ በ100 ብር ለገበያ ቀርቧል፡፡
Saturday, 21 May 2016 16:32
Published in
ኪነ-ጥበባዊ ዜና