Saturday, 21 May 2016 14:43

የኢትዮጵያ አየር መንገድ “የአመቱ የአፍሪካ ምርጥ ሽልማት”ን አገኘ

Written by 
Rate this item
(4 votes)

የኢትዮጵያ አየር መንገድ የአፍሪካን አቪየሽንን የ2016 የአፍሪካ ምርጥ አየር መንገድ ሽልማት ሰሞኑን በደቡብ አፍሪካ ጆሃንስበርግ በተካሄደ ስነ-ስርዓት መቀበሉን ትናንት ባወጣው መግለጫ አስታወቀ፡፡
አየር መንገዱ በፋይናንስ እንቅስቃሴና ትርፋማነት፣ በረራን በማዘመን፣ የበረራ መስመር ትስስርን በማስፋፋት፣ በአጠቃላይ የደንበኞች እንክብካቤና በአህጉሪቱ የአቪየሽን ኢንዱስትሪ ልማት አስተዋጽኦ በማበርከት ረገድ በአመቱ ባስመዘገበው የላቀ ውጤት ለሽልማት መብቃቱ ተነግሯል፡፡
በስነስርዓቱ ላይ ተገኝተው ሽልማቱን የተቀበሉት የአየር መንገዱ ቺፍ ኦፐሬቲንግ ኦፊሰር አቶ መስፍን ጣሰው፤ ሽልማቱ አየር መንገዱ ላለፉት 70 አመታት አፍሪካን አንድ ለማድረግና ከተቀረው አለም ጋር ለማቀራረብ በቁርጠኝነት መስራቱን የሚያረጋግጥ ነው ብለዋል፡፡ ሽልማቱን ያበረከቱት የአፍሪካን አቪየሽን ዋና ስራ አስፈጻሚ ኒክ ፋዱግባ በበኩላቸው፣ የኢትዮጵያ አየር መንገድ ተጨባጭ ውጤቶችን በማስመዝገብ መሪነቱን ይዞ መቀጠሉንና ለአፍሪካ ትልቅ የኩራት ምንጭ መሆኑን በሽልማት ስነስርዓቱ ላይ ተናግረዋል፡፡

Read 1980 times