Saturday, 21 May 2016 13:15

“በስኳር ፕሮጀክቶች ላይ “ሜቴክ” ምላሽ ሰጠ

Written by 
Rate this item
(9 votes)

    የብረታ ብረትና ኢንጅነሪንግ ኮርፖሬሽን ዋና ዳይሬክተር ሜጀር ጀነራል ክንፉ ዳኘው የሜቴክ
ፕሮጀክቶችን የሚያስቃኝ ዘጋቢ ፊልም ከትናንት በስቲያ በተመረቀበት ወቅት ስኳር ፕሮጀክቶችን
አስመልክቶ በተለይ በአዲስ አድማስ ለቀረበላቸው ጥያቄ ምላሽ ሰጥተዋል፡፡ዘጋቢ ፊልም መስራት ያስፈለገበት ምክንያት መነሻው ምንድነው?
ጥናት ሰርቼ ነበር፡፡ የታገልኩለት ስለሆነ ጥናት ሰርቼ ጽሑፍ ያዘጋጀሁት፡፡ ጽሑፉ፣ ከጋዜጠኛዋ ፍፁም የሺጥላ የዘጋቢ ፊልም መነሻ ሀሳብ ጋር በጣም የተቀራረበ ስለነበር ጽሑፉን ሰጠኋት ያንን የማዳበር ስራ፤ ከመስራት በስተቀር ተነሳሽነቱ የጋዜጠኛዋ ነው፡፡ዘጋቢ ፊልሙ ለመስራት ምን ያህል ጊዜና ገንዘብ ወሰደ? ፊ ልሙን ላይ፤ የብረታብረት ኮርፖሬሽን ስራዎች ሁሉውጤታማ እንደሆኑ ተገልጿል፡፡ ሁሉም ነገር ጥሩ ነው ተብሏል፡፡ ግን በፓርላማ እና በተለያዩ ሚዲያዎች ላይ ደግሞ፣ በተለይ ከስኳር ፕሮጀክቶች ጋር በተያያዘ አገሪቱ ለብዙ ወጪ ተዳርጋለች ተብላችሁ ተተችታችኋል፡፡ የመጀመሪያውን ጥያቄ ስንመለከት፣ ፊልሙን ያዘጋጁዜጐች፣ ከፊልሙ የጽሑፍ ዝግጅት ጀምሮ፣ በቀረፃ እና በመሰል ጉዳዮች ላይ ሲሰሩ ከሶስት  ወር በላይ ሳይወስድ አይቀርም፡፡ መነሻ ሃሳቦቹ ከዚያ ቀደም ይላሉ፡፡ ብዙም ደክመውበታል፡፡ሁለተኛ ጥያቄሽን በተመለከተ፣ በዋናነት ማለት የምፈልገው፣ ምንም ክስ ቢነሳም፣ ለእኔ ትልቁ ነገር የኢትዮጵያ መንግስት የጀመረውና የሚመራው የኢኮኖሚ ልማት አቅጣጫ፣ የሚሳካ መሆኑ ነው፡፡ በአንዳንድ ሰዎች ክስ ቢነሳም፣ ድክመታችንን የሚያሳይ አይደለም፡፡ በዚያው ልክ፣ ንካሬያችንንም የሚያሳይ አይደለም፡፡ዋናው ጉዳይ እኛ ድክመት ቢኖርብንም ባይኖርብንም፣ የልማታዊ ኢኮኖሚ አቅጣጫ አይቆምም፡፡ የኢትዮጵያ ህዝቦች ያድጋሉ፡፡ እኔ ካጠፋሁ ልቀጣ እችላለሁ፡፡ ተቋማት ግን ይቀጥላሉ፤ መቀጠልም አለባችሁ፡፡ በዚሁ አጋጣሚ፣ በግሌ አስተያየት፣ ስኳር ኮርፖሬሽን ውድቀት
አለው ብዬ አላምንም፡፡ ስኳር ኮርፖሬሽን የወደቀበት ምክንያት በእንቶኔ ነው በእከሌ ነው
ቢባልም፣ አይገባኝም፡፡

Read 6154 times