Saturday, 30 April 2016 11:48

የሀገረሰብ ሕክምና ታሪክ ለኅትመት በቃ

Written by 
Rate this item
(2 votes)

“የኢትዮጵያ ባህላዊ መድኃኒትና ሕክምና የምዕተ ዓመት ጉዞ” የተሰኘ መጽሐፍ ሰሞኑን ለንባብ በቅቷል። መጽሐፉ በዐይነቱም ሆነ በጥልቀቱና በይዘቱ የተለየና የመጀመሪያው ነው የተባለ ሲሆን ለረጅም ጊዜ ተዘንግቶ የኖረውን የሀገረሰብ ህክምና ታሪክ በማጐልበት ረገድ ከፍተኛ ድርሻ እንዳለው ተገልጿል፡፡ አዘጋጁ ዶክተር ባልቻ አሰፋ ከተለያዩ የሚኒስቴር መስሪያ ቤቶች በርካታ የቃልና የጽሑፍ ማስረጃዎችን፣ 63 ያህል የሀገረሰብ ህክምና ባለመያዎችን ቃለ ምልልሶችና ሌሎች በርካታ ግብአቶችንም ተጠቅመዋል፡፡ በ10 ምዕራፍ የተከፋፈለውና በ377 ገፆች የተቀነበበው መጽሐፉ፣ በ150 ብር ዋጋ ለገበያ ቀርቧል፡፡

Read 1436 times