Saturday, 23 April 2016 10:04

ታንዛኒያና እና ኬንያ በኢትዮጵያውያን ስደተኞች ጉዳይ እየተወዛገቡ ነው

Written by 
Rate this item
(6 votes)

ድንበሬን በህገ ወጥ መንገድ አቋርጠዋል በሚል ታንዛኒያ የእርስ ፍርድ ወስናባቸው የቅጣት ጊዜያቸውን ያጠናቀቁ 74 ኢትዮጵያውያንን በኬንያ ድንበር ላይ ማራገፏ በሁለቱ አገራት መካከል ውዝግብ መፍጠሩን “ዘ ስታንዳርድ” የተባለው የኬንያ ጋዜጣ ዘግቧል፡፡  
የታንዛኒያ መንግስት ኢትዮጵያውያኑ ስደተኞች እስራቸውን ከጨረሱ በኋላ ወደ ኢትዮጵያ መመለስ ሲገባው በኬንያ ድንበር ላይ በሚገኝ በረሃ ላይ መጣሉ አግባብ አይደለም ሲል የወቀሰው የኬንያ መንግስት፤ ኢትዮጵያውያኑን ወደ ታንዛኒያ መልሶ እንደሚልክ አስታውቋል፡፡
“ኬንያ የታንዛኒያን ችግር የምትሸከምበት ምክንያት የለም፤ አለማቀፍ ህግም ይህን አይፈቅድም” ብሏል፤ የኬንያ መንግስት - “ዘ ስታንዳርድ” እንደዘገበው፡፡

Read 1918 times